01/12/2025
ኢሠማኮ እና የቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማኅበራት ፌዴሬሽን የጋራ ሥራ መግባቢያ ስምምነት (MoU) ተፈራረሙ
ኢሠማኮ እና የቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማኅበራት ፌዴሬሽን ግንኙነታቸውን በማጠናከር ለወደፊት አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የጋራ ሥራ መግባቢያ ስምምነት (MoU) ህዳር 20/2018 ዓ.ም ተፈራረሙ፡፡
የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ስምምነቱ ያለውን ጠቀሜታ ሲገልጹ በቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን እና በኢሠማኮ የክልል ቅርንጫፎች መካከል የተፈረመው ስምምነት ያላቸውን የወዳጅነት ትብብር፣ እውቀት ሽግግርና የአብሮነት መሰረት በማጠናከር በትብብር ለመሥራት ነው ብለዋል።
የመግባቢያ ሰነዱ በሀለቱ ወገኖች መካከል ቀጥተኛ የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዲመሰረት እና በመሠረታዊ የሠራተኛ ማኅበራት መካከል የልምድ ልውውጥ እና ትብብር እንዲፈጠር በማበረታታት በቀጣይም በሁለቱም ሀገሮች ሠራተኞች ፍላጎት ላይ ያተኮሩ የአቅም ግንባታ ፕሮግራሞች የልምድ ልውውጦችና እና ገንቢ ውይይቶች እንደሚካሄዱ በስምምነቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በኢሠማኮ በኩል ስምምነቱን የተፈራረሙት አቶ ድሪብሳ ለገሰ የኢሠማኮ ኢንዱስትሪ ግንኙነትና ማህበራት ማደራጃ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ናቸው፡፡
በሌላ በኩል የቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማኅበራት ፌዴሬሽን ተወካዮች ከአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች፤ የሠራተኛውን መብት ለማስጠበቅ ከኢሠማኮ ጋር በጋራ የሚያከናውኗቸውን ተግባራት እና የኢንዱስትሪ የኢንዱስትሪ ግንኙነትን አስመልክቶ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡