Confederation of Ethiopian Trade Unions/ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • Confederation of Ethiopian Trade Unions/ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን

Confederation of Ethiopian Trade Unions/ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን CETU is the confederation of ethopian trade union! it stands for worker's right and benefits!!!

የኮንፌደሬሽኑ ስትራቴጂክ አቅጣጫ
በዚህ ክፍል በአምስት አመታት ትኩረት ሊደርግባቸው የሚገቡና መሻሻል ያለባቸው አካባቢዎች የሚያሳዩ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎች ተለይተው ቀርበዋል፡፡ የተለዩት ጉዳዮች ኮንፌደሬሽኑ የተሰጠውን ተልዕኮ ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመወጣት የትኩረት አቅጣጫዎች የሚከተል ይሆናል፡፡
3.1. ራዕይ፤ ተልዕኮና ዕሴቶች
ራዕይ
የሥራ ዋስትናዉ የተረጋገጠ፤ የሙያ ደህንነቱና ጤንነቱ የተጠበቀ፤ የሥራ ባህሉና ምርታማነቱ የዳበረ፤ ኑሮዉ የተሻሻለ የሠራተኛ መደብ የተፈጠረባት የለማች ኢትዮጵያን ማየት፡፡
ተልዕኮ
ሠራተኛዉን በማህበር በማደራጀትና ሁለንተናዊ አቅሙን በመገንባት መብትና ጥቅሙን እንዲያከብር ማድረግና ማስከ

በር፤ በሀገሪቱ ፖለቲካዊ፤ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች በተለይም በዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ዲሞክራሲያዊ ባህል መዳበር ላይ ትርጉም ያለዉ ተሳትፎ በማድረግ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት፡፡
እሴቶች
 ሰባዊነት
 ቁርጠኝነት
 ዴሞክራሲያዊ ባህል
 ኢንዱስትሪ ሰላም
 ማህበራዊ ምክክሮሽ
 ምቹ የስራ ሁኔታ

01/12/2025

ኢሠማኮ እና የቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማኅበራት ፌዴሬሽን የጋራ ሥራ መግባቢያ ስምምነት (MoU) ተፈራረሙ
ኢሠማኮ እና የቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማኅበራት ፌዴሬሽን ግንኙነታቸውን በማጠናከር ለወደፊት አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የጋራ ሥራ መግባቢያ ስምምነት (MoU) ህዳር 20/2018 ዓ.ም ተፈራረሙ፡፡
የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ስምምነቱ ያለውን ጠቀሜታ ሲገልጹ በቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን እና በኢሠማኮ የክልል ቅርንጫፎች መካከል የተፈረመው ስምምነት ያላቸውን የወዳጅነት ትብብር፣ እውቀት ሽግግርና የአብሮነት መሰረት በማጠናከር በትብብር ለመሥራት ነው ብለዋል።
የመግባቢያ ሰነዱ በሀለቱ ወገኖች መካከል ቀጥተኛ የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዲመሰረት እና በመሠረታዊ የሠራተኛ ማኅበራት መካከል የልምድ ልውውጥ እና ትብብር እንዲፈጠር በማበረታታት በቀጣይም በሁለቱም ሀገሮች ሠራተኞች ፍላጎት ላይ ያተኮሩ የአቅም ግንባታ ፕሮግራሞች የልምድ ልውውጦችና እና ገንቢ ውይይቶች እንደሚካሄዱ በስምምነቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በኢሠማኮ በኩል ስምምነቱን የተፈራረሙት አቶ ድሪብሳ ለገሰ የኢሠማኮ ኢንዱስትሪ ግንኙነትና ማህበራት ማደራጃ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ናቸው፡፡
በሌላ በኩል የቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማኅበራት ፌዴሬሽን ተወካዮች ከአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች፤ የሠራተኛውን መብት ለማስጠበቅ ከኢሠማኮ ጋር በጋራ የሚያከናውኗቸውን ተግባራት እና የኢንዱስትሪ የኢንዱስትሪ ግንኙነትን አስመልክቶ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡

37ኛው የአለም አቀፉ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ITUC) ምክርቤት ስበሰባ በአዲስ አበባ  ይካሄዳልበአሠማኮ አስተባባሪነት ከህዳር 20-25/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚካሄዱትና በ...
01/12/2025

37ኛው የአለም አቀፉ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ITUC) ምክርቤት ስበሰባ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
በአሠማኮ አስተባባሪነት ከህዳር 20-25/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚካሄዱትና በርካታ እንግዶች ስለሚያሳተፉባቸው ታላላቅ አለምአቀፍና አህጉራዊ ስብሰባዎችን በተመለከተ የኢሠማኮ የኢንዱስትሪ ግንኙነትና ማህበራት ማደራጃ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ድሪብሳ ለገሰ ዛሬ ህዳር 19/2018 ዓ.ም ኢሠማኮ ህንፃ 3ኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ፡፡
አቶ ድሪብሳ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ከህዳር 23 እስከ ህዳር 25 2018 ዓ.ም የአለም አቀፉ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ITUC) ምክርቤት ስበሰባ፣ የቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማኅበራት ፌዴሬሽን ተወካዮች አዲስ አበባ መጥተው የሚያደርጉት የሥራ ጉብኝት ነው፡፡ ዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ITUC) እና ኦል ሰብ ሰሃራን አፍሪካ በጋራ የሚያዘጋጁትን ስብሰባ እንዲሁም የአፍሪካ ቀንድ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (HACTU) የሚያከናውኗቸውን ስብሰባዎች ኃላፊነት ወስዶ በአዲስ አበባ ከተማ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ይህን ዓለም አቀፍ ስብሰባ በአዲስ አበባ እንዲካሄድ ምክንያት የሆነው ኢሠማኮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ተቀባይነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎላ በመምጣቱ ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም የቻይና ቤጂንግ የሠራተኛ ማኅበራት ፌዴሬሽን የሚያደርጉት የሥራ ጉብኝት እና ዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ITUC) እና ኦል ሰብ ሰሃራን አፍሪካ በጋራ የሚያዘጋጁትን ስብሰባ በኮንፌዴሬሽኖቹ መካከል የልምድ ልውውጥ እና መልካም የሥራ ግንኙነት ለመፍጠር እንደሆነ ተገልጿል፡፡

በመሆኑም እነዚህን በርካታ እንግዶች የሚያሳተፉባቸውን ታላላቅ አለምአቀፍና አህጉራዊ ስብሰባዎች በተመለከተ አርብ ህዳር 19/2018 ዓ.ም ኢሠማኮ ህንፃ 3ኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ስለሚሰጥ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ በቦታው በመገኘት የሚዲያ ሽፋን እንድትሰጡልን፤
እንዲሁም ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በሚካሄደው የአለም አቀፉ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ITUC) ምክርቤት የመክፈቻ ስነ-ሥርዓት ላይ ከጧቱ 2፡30 በመገኘት የሚዲያ ሽፋን እንድትሰጡልን የተለመደ ትብብራችሁን እንጠይቃለን፡፡

ኢሠማኮ ለሠራተኞቹ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን በሥራ ስነ-ምግባርና ተቋማዊ ባህልን ማዳበር እና በፀረ ሙስና አዋጅ በሚሉ ሁለት ርዕሶች ከህዳር 4-6...
22/11/2025

ኢሠማኮ ለሠራተኞቹ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን በሥራ ስነ-ምግባርና ተቋማዊ ባህልን ማዳበር እና በፀረ ሙስና አዋጅ በሚሉ ሁለት ርዕሶች ከህዳር 4-6/2018 እና ከህዳር 11-13/2018 ዓ.ም በሁለት መርሃ-ግብሮች ለኮንፌዴሬሽኑ ሠራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ፡፡
የኢሠማኮ ጥናት፣ ምርምር፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ድሪባ ስለ ስልጠናው ዓላማ በሰጡን አስተያየት ስልጠናው አቅም ግንባታ በመሆኑ ሠራተኞች በሚሠሩበት ቦታ የተሻለ ቅልጥፍና እና አመለካከት እንዲኖራቸው ያግዛል ብለዋል፡፡ በተለይም ከሙያ ስነ ምግባር ጋር የተያያዘው ስልጠና ሠራተኛው ደንበኛውን በትክክል ለማገልገል የሚችለው ሙያዊ ስነ ምግባር ሲኖረው በመሆኑ ሁሉም በተሰማራበት መስክ የራሱን አስተዋፅኦ እንዲያበረክትና የተሻለ አፈጻጸም እንዲኖረው ለማድረግ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት አቶ ሲሳይ በፍቃዱ ከአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ የስነ ምግባር ዳይሬክተር እና ወ/ሮ መኪያ ዲና ከአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ አቃቤ ሕግ መሆናቸውንም ለማወቅ ችለናል፡፡

የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ የዓለም ሥራ ድርጅት የስልጠና ማዕከል (ITCILO) የአመራር ቦርድ አባል ሆነው እንደተመረጡ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የማዕከሉ የቦርድ አባላት በስዊዘ...
22/11/2025

የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ የዓለም ሥራ ድርጅት የስልጠና ማዕከል (ITCILO) የአመራር ቦርድ አባል ሆነው እንደተመረጡ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የማዕከሉ የቦርድ አባላት በስዊዘርላንድ ጄኔቭ የሚያካሂዱትን ስብሰባ የሚያሳይ ፎቶ

የጨርቃ ጨርቅ ቆዳና ልብስ ስፌት ሠራተኛ ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ምርጫ አካሄደ የጨርቃ ጨርቅ ቆዳና ልብስ ስፌት ሠራተኛ ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈጻሚና የኦዲት ኮሜቴ የ...
22/05/2025

የጨርቃ ጨርቅ ቆዳና ልብስ ስፌት ሠራተኛ ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ምርጫ አካሄደ
የጨርቃ ጨርቅ ቆዳና ልብስ ስፌት ሠራተኛ ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈጻሚና የኦዲት ኮሜቴ የሥራ ዘመን በመጠናቀቁ ምክር ቤቱ ግንቦት 12 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው 14ኛው ጠቅላላ ጉባዔ አዲስ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና አዲስ የኦዲት ኮሚቴ ምርጫ አከናወነ፡፡
ጉባዔው አቶ ተስፋዬ አብዲሳን የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት፣ ወ/ሮ ሻሺቱ ማሞን ምክትል ፕሬዚዳንት፣ አቶ ይማም ሁሴንን የማኅበራት ማደራጃና ኢንዱስትሪ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ እንዲሁም አቶ ተክሉ ሸዋረጋን አስተዳደርና ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አድርጎ ሲመርጥ አቶ ሰለሞን አባተን የኦዲት ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ ወ/ሮ ሀና ገረሱን ፀሐፊ፣ ወ/ሮ ለይላ ተሰማን ደግሞ አባል አድርጎ መርጧል፡፡
ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የኢሠማኮ የኢንዱስትሪ ግንኙነትና የማኅበራት ማደራጃ ዘርፍ ም/ፕሬዝዳንት አቶ ድሪብሳ ለገሰ የሠራተኛ ማኅበር አባል ያልሆኑ ሠራተኞችን ማካተት እና የሠራተኛውን አንድነት ማጠናከር ካልተቻለ ውጤታማ ሥራ መስራት ስለማይቻል አባል ያልሆኑ ሠራተኞችን ወደ አባልነት ለማምጣት ጠንክረን ልንሠራ ይገባል ብለዋል፡፡ ያልተደራጁ ሠራተኞች ከአሠሪዎች ጋር በመወገን የሚያሳድሩት ተፅዕኖ እጅግ ከባድ ስለሆነ ህብረት አሰፈላጊ ነው፡፡ የኛ ጥንካሬ የሚለካው በመደራጀታችን ልክ ነው ያሉት አቶ ድሪብሳ በፌዴሬሽንም ይሁን በመሠረታዊ የሠራተኛ ማኅበር ደረጃ ማደራጀት ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበዋል፡፡
በሌላ በኩል ግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም በተካሄደው 55ኛ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ የፌዴሬሽኑን የ6 ወራት ሪፖርት ያቀረቡት አቶ ተስፋዬ አብዲሳ ከማህበራት በሚቀርቡላቸው የአግዙን ጥያቄዎች መሠረት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸው፤ በኮሪደር ልማት ምክንያት ድርጅታቸው ለፈረሰባቸው ሠራተኞች የአዲስ አበባ ከንቲባ ቢሮ ድረስ በመሄድ መጠየቃቸውን፣ ሠራተኞች በሥራ ላይ ስለሚደርስባቸው አደጋ፣ የሥራ ውላቸው ያለ አግባብ ለተቋረጠባቸው ሠራተኞች ፣የህብረት ስምምነት ጥሰት ላጋጠማቸው ማኅበራት፣ የማህበር አመራር በመሆናቸው ከስራቸው ለታገዱ ወደ ሥራ ገበታቸው እንዲመለሱ በማድረግ፣ የህብረት ስምምነት ድርድርን በማዘግየት የሠራተኛውን መብት እንዳይከበር የሚሰሩ ድርጅቶች በአካል ሄዶ በማወያየት እና ሌሎችም ከሠራተኛው መብት መጠበቅ ጋር የተያያዙ በፌዴሬሽኑ የተከናወኑ በርካታ ተግባራትን አንስተዋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት ባነሱት ሀሳብ ስልጠናን በተመለከተ አፈጻጸሙ ከእቅድ በላይ መሆኑ የሚያስመሰግን ቢሆንም አሰጣጡ ሁሉንም ማዕከል ያደረገ ባለመሆኑ ለአዳዲስ አመራሮች ስልጠና አልተሰጠም፡፡ ተደራሽነታችሁ ሰፊ ስላልሆነ ራቅ ያሉ አባላት ተጠቃሚ መሆን የሚችሉበት ሁኔታ ቢብራራ፡፡ በአዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ይህን ያህል ማህበር ከፌዴሬሽን ሲወጣ ቀለል አድርጎ በሪፖርት ማቅረብ ብቻ ሳይሆን ጉዳዩ በጥልቀት ተመርምሮ ችግሮችን ለመፍታት እንዴት አልተቻለም፡፡ በአሁኑ ሰዓት የሠራተኛው አንገብጋቢ ችግር የዝቅተኛ ደሞዝ ወለል መወሰንና ከሠራተኛው የሚቆረጠው የገቢ ግብር እንዲቀነስ ቢሆንም ሪፖርቱ ስለዚህ ጉዳይ ያነሳው ነገር የለም፡፡ አዳዲስ ማኅበራትን ከማፍራት አንጻር ያልተጠቀምንባቸው አካባቢዎች አሉ ትኩረት አድርጋችሁ ብትሰሩ የሚሉና ሌሎችንም በርካታ ሃሳቦች አንስተዋል፡፡
በመጨረሻም የኢሠማኮ የህዝብና ውጭ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ በሰጡት አስተያየት የምናገለግለው ሠራተኛውን ነው፡፡ ኢሠማኮም በሠራተኛው ጉዳዮች ላይ አይደራደርም፤ሠራተኛው ያልተፈታ በርካታ ችግር አለበት፡፡ ስለዚህ ምክር ቤቱ የፌዴሬሽኑ

በአገራችን በየጊዜው እየጨመረ ያለው የነዳጅ ዋጋ ሠራተኛውን የከፋ ችግር ውስጥ እያስገባው ነው የሀገር አቀፍ ንግድ፣ ቴክኒክና ህትመት ኢንዱስትሪ ሠራተኛ ማህበራት ፌዴሬሽን 51ኛ መደበኛ የም...
15/05/2025

በአገራችን በየጊዜው እየጨመረ ያለው የነዳጅ ዋጋ ሠራተኛውን የከፋ ችግር ውስጥ እያስገባው ነው
የሀገር አቀፍ ንግድ፣ ቴክኒክና ህትመት ኢንዱስትሪ ሠራተኛ ማህበራት ፌዴሬሽን 51ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባውን አካሄደ፡፡
በአገራችን በየጊዜው እየጨመረ ባለው የነዳጅ ዋጋ ምክንያት ሠራተኛው የኑሮ ውድነቱን መቋቋም ባለመቻሉ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት የችግሩን አሳሳቢነት ተረድተው መፍትሄ ካልሰጡ ሠራተኛውን የከፋ ችግር ውስጥ እንደሚያስገባው የሀገር አቀፍ ንግድ፣ ቴክኒክና ህትመት ኢንዱስትሪ ሠራተኛ ማህበራት ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ደበሌ ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም በተካሄደው የፌዴሬሽኑ 51ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት ገልጸዋል፡፡
የኢሠማኮ ኢንዱስትሪ ግንኙነት ም/ፕሬዝዳንት አቶ ድሪብሳ ለገሰ በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት አደረጃጀታችንን እና ህብረታችንን አጠናክረን ጫና መፍጠር ካልቻልን አሁን እየደረሰብን ካለው ችግር በላይ እንደሚደርስብን ማወቅ ይገባናል፡፡ በአንዳንድ ክልሎች ከአቅም በላይ በሆነ ሁኔታ ማደራጀት አስቸጋሪ ቢሆንም ባለንበት ቦታ አንድነታችንን የሚጠይቁ በርካታ ተግዳሮቶች በመቋቋም ኢሠማኮ ከፌዴሬሽኖች ጋር በመሆን እያከናወናቸው ያሉትን ሥራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ቃል ገብተዋል፡
አክለውም የኢሠማኮ ጠቅላይ ምክር ቤት ያስተላለፋቸውን ውሳኔዎች መሰረት በማድረግ የሠራተኛውን ዋና ዋና ጥያቄዎች በተለይም ከሠራተኛው የሚቀነሰው የሥራ ግብር ምጣኔ እንዲሻሻል እና የመነሻ ደሞዝ ወለል የሚወስን ቦርድ እንዲቋቋም የሚሉትን ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩን በአካል ከማነጋገር ጀምሮ የሚመለከታቸው አካላት ጋ በመድረስ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም እያቀረበ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ደበሌ ባቀረቡት ሪፖርት በድርጅታቸው አለመግባባት ገጥሟቸው የአግዙን እገዛ ጥያቄ ላቀረቡ ማኅበራት ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ በማድረግ፣ በህገወጥ መንገድ የሥራ ውላቸው የተቋረጠባቸው ሠራተኞች ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ ወይም በህጉ መሰረት የሚገባቸው ክፍያ ተከፍሏቸው እንዲሰናበቱ እንዲደረግ ፌዴሬሽኑ እገዛ አድርጓል፡፡ እንዲሁም በመለዋወጫ ችግር ምክንያት ድርጅቶች ሲዘጉ ሠራተኞች በህጉ መሠረት አስፈላጊው ክፍያ ተፈጽሞላቸው እንዲሰናበቱ እንዲደረግ፣ አለአግባብ ከሥራ ቦታቸው የተዘዋወሩ የማኅበር አመራሮች ወደ ነበሩበት የሥራ ቦታቸው እንዲመለሱ በመጠየቅ፣ ከደሞዝ ጭማሪ አፈጻጸም ጋር የተፈጠረ አለመግባባትን ለመፍታት ከድርጅቱ ማኔጅመንት ጋር በመወያየት መፍትሔ እንዲፈልጉ በመጠየቅ እና ሌሎችንም ከሠራተኛ መብት ጋር የተያያዙ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አብራርተዋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት ባነሱት ሃሳብ ከጥሬ ዕቃ አቅርቦት ማነስ ጋር በተያያዘና በኮሪደር ልማት ምክንያት ድርጅቶች እየፈረሱ በመሆናቸው ሠራተኛው የመበተን አደጋ እየገጠመው ነው፡፡ ፌዴሬሽኑ በዚህ በኩል ፌዴሬሽኑ ምን እያደረገ ነው? ኢሠማኮ ጥያቄዎችን ከማቅረብ ባለፈ ሌሎች አማራጮችን ሊወስድ ይገባል፤ድርጅቶች ሲዋሀዱ የማኅበራት መዋጮ በምን መልክ መሆን እንዳለበት እገዛ ቢደረግልን የሚሉና ሌሎችንም በርካታ ሀሳቦች አንስተዋል፡፡
በተነሱት ሃሳቦች ዙሪያ ምላሽ የሰጡት የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ደበሌ ማኅበራት ላይ ጉብኝት በማድረግ ያለባቸውን ክፍተት በመለየት የስልጠና ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸው ለመንግስት የቀረበውን ጥያቄ በተመለከተ የኑሮ ውድነቱ በከፍተኛ ደረጃ ቢጨምርም በአንጻሩ ለሠራተኛው የተደረገለት ማካካሻ ባለመኖሩ ሠራተኛው በኑሮ ውድነቱ ከመ

የአገር አቀፍ እርሻ እና አግሮ ኢንዱስትሪ ሠራተኛ ማህበራት ፌዴሬሽን 57ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባውን አካሄደየአገር አቀፍ እርሻ እና አግሮ ኢንዱስትሪ ሠራተኛ ማህበራት ፌዴሬሽን ትናንት...
09/05/2025

የአገር አቀፍ እርሻ እና አግሮ ኢንዱስትሪ ሠራተኛ ማህበራት ፌዴሬሽን 57ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባውን አካሄደ
የአገር አቀፍ እርሻ እና አግሮ ኢንዱስትሪ ሠራተኛ ማህበራት ፌዴሬሽን ትናንት ሚያዝያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም 57ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባውን 11ኛ ፎቅ በሚገኘው የኢሠማኮ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄደ፡፡
የኢሠማኮ ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የሠራተኞችን የመደራጀት ምጣኔ ለማሳደግ በ2017 ዓ.ም ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር ባወጡት ዕቅድ መሰረት የክልል ቢሮዎችን በማካተት ፕሮግራም በመቅረጽ፤ ከኢሠማኮ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር ለመሥራት መመሪያ መተላለፉን ገልጸዋል፡፡ በተወሰኑ ክልሎች ላይ አብሮ ከመሥራት ጋር በተያያዘ ወደ ኋላ የመቅረት ነገር እንደሚታይ የገለጹት አቶ ካሳሁን አንዳንድ አሠሪዎች መደራጀትን ቢፈቅዱም ከማኅበሩ ጋር ለመሥራት ፍቀደኛ አለመሆን፣ ህብረት ስምምነት ያለመደራደር እንዲሁም ድርድር ከጀመሩ በኋላ ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ የማድረግና ከተደራደሩም በኋላ ያለመፈጸም ችግር እንዳለ ተናግረዋል፡፡ አክለውም የምክር ቤቱ አባላት አንድነታቸውን በማጎልበት በየድርጅታቸው ያለውን ሠራተኛ የማኅበር አባል እንዲሆን ጠንክረው መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ገበየሁ አዱኛ ለምክር ቤቱ ፌዴሬሽኑ ያከናወናቸውን በርካታ ተግባራት በሪፖርታቸው ላይ ዘርዝረዋል፡፡ ፌዴሬሽኑ በማህበራዊ ምክክሮሽ፣ በኢንዱስትሪ ግንኙነት እና አዳዲስ ማህበራትን በማደራጀት ሰፊ ሥራ መሰራቱንም በሪፖርታቸው አካተዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ በተለይ በአሁኑ ሰዓት ያለው የጸጥታ ችግር በሠራተኛውና በቤተሰቡ ላይ እየፈጠረ ያለው ችግር ፌዴሬሽኑ በስጋት የሚመለከተው መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አቶ ገበየሁ በታጠቁ ኃይሎች ምክንያት ግድያዎች አፈናና ዝርፊያ በሠራተኛውና በቤተሰቡ ላይ እያደረሰ ያለውን ችግር አስመልክተው በየደረጃው ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ማሳወቃቸውን በዚህ ሪፖርታቸው አብራርተዋል፡፡ ይህ ውድመትና ጥፋት ታባብሶ መቀጠሉ ለድርጅቶች ህልውና አስጊ በመሆኑ የሠራተኞች የሥራ ዋሰትና ለከፋ አደጋ መዳረጉንም አስረድተዋል፡፡
ምክር ቤቱ ፌዴሬሽኑ በባለሙያ አስጠንቶ ባቀረበው አዲስ የደመወዝ ስኬል ጥናት እና የተመራጮችን አዲስ የአስተዳደር መመሪያ ላይ ሰፊ ውይይት አድርጎ ሁለቱንም አጀንዳዎች በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

ኢሠማኮ ላቀረባቸው ዋና ዋና የሠራተኛው ጥያቄዎች መንግሥት ምላሽ ባለመስጠቱ  በሠራተኛው ኑሮ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነውየኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎኢሠማኮ በተከታታይ መንግስት ም...
02/05/2025

ኢሠማኮ ላቀረባቸው ዋና ዋና የሠራተኛው ጥያቄዎች መንግሥት ምላሽ ባለመስጠቱ በሠራተኛው ኑሮ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነው
የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ
ኢሠማኮ በተከታታይ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥባቸው ላቀረባቸው ዋና ዋና የሠራተኛው ጥያቄዎች ምላሽ ባለመሰጠቱ የኑሮ ውድነቱ በሠራተኛው ኑሮ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነው ሲሉ የተናገሩት የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ከአንድ አመት በፊት ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በነበራቸው ውይይት በሚመለከታቸው ሚኒስትር መሥሪያ ቤቶች በኩል ምላሽ እንዲሰጥ አቅጣጫ ቢሰጡም እስካሁን ምላሽ እንዳልተገኘ ገልጸዋል፡፡
አክለውም የኑሮ ውድነቱ በሠራተኛው ላይ ከፍተኛ ጫና እያሰደረ በመሆኑ ከደመወዝ የሚቆረጠው የሥራ ግብር ምጣኔ እንዲቀነስልን፣የዝቅተኛ ደመወዝ ወለል የሚወስን ቦርድ እንዲቋቋም፣የሠራተኞች በነጻነት የመደራጀት መብት እንዲከበር፣ የሥራ አካባቢ ደህንነትና ጤንነትን ለመጠበቅ ተገቢው ሥራ እንዲሰራ፣ የዓለም ሥራ ድርጅት ያወጣቸው ስምምነቶች ቁጥር 97፣143፣190፣እና 189ን አገራችን ተቀብላ እንድታፀድቅ፣ተጨማሪ ክፍያ ከሠራተኛው ደመወዝ መቁረጥ የበለጠ ኑሮውን ስለሚያከብደው እንደገና እንዲታይ፣ በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶችና ጦርነቶች በውይይት እንዲፈቱ ጥረት እንዲደረግ እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሠራተኛውን ለማወያየት መድረክ እንዲያመቻቹላቸው ለመንግስት ጥያቄያቸውን አቅርበዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ዘርፍ ሚኒስቴር ደኤታ አቶ ዳንኤል ተሬሳ በበኩላቸው መንግስት እንደ ሀገር ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና ለመቀነስ ከፍተኛ በጀት በመመደብ በአጠቃላይ ዝቅተኛ ገቢ ላላው ማኅበረሰብ በተለይ ለሠራተኛው ድጎማ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታቸው ሰላማዊ ኢንዱስትሪና የኢንዱስትሪ ባህል ግንባታ እንዲረጋገጥ ምቹ የሥራ ቦታ እንዲፈጠርና የሠራተኛውና የአሠሪው በነጻነት የመደራጀት መብት በማረጋገጥ ሠራተኛው ከአሠሪው ጋር የመመካከር እንዲሁም ግዴታውን እየተወጣ መብትና ጥቅሙ እንዲከበር ከኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ጋር በጋራ በማቀድ ሥራዎችን በመገምገም የቅንጅት ሥራውን በማጠናከር ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
የዘንድሮው የአለም የሠራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) በዓል የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ፣ አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ዘርፍ ሚኒስቴር ደኤታ፣ የአለም ሥራ ድርጅት ተወካይ፣ የኢሠማኮ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የ9ኙም ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ሬዝዳንቶች እንዲሁም ከተለያዩ ድርጅቶች ተወክለው የመጡ የሠራተኛው ተወካዮች በተገኙበት “መንግስት ላቀረብናቸው ጥያቄዎች አስቸኳይ ምላሽ ይስጠን” በሚል መሪ ቃል ሚያዝያ 23/2017 ዓም በኢሠማኮ ጊቢ ውስጥ በድምቀት ተከብሮ ውሏል፡፡ በተጨማሪም በዓሉ ኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ በሚገኘው አበበ ቢቂላ ስታደየም በተደረገው የሜይ ዴይ የጥሎ ማለፍ ሻምፒዮና ስፖርታዊ ውድድር እና በስምንት የኢሠማኮ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በፓናል ውይይት ተከብሮሯል፡፡

የሠራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) መታሰቢያ የጥሎ ማለፍ ውድድር በአዳማ ከተማ በሚካሄድ የእግር ኳስ የዋንጫ ጨዋታ እንደሚጠናቀቅ ተገለጸመጋቢት 6 የተጀመረው የአለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን (ሜይ ዴ...
17/04/2025

የሠራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) መታሰቢያ የጥሎ ማለፍ ውድድር በአዳማ ከተማ በሚካሄድ የእግር ኳስ የዋንጫ ጨዋታ እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ
መጋቢት 6 የተጀመረው የአለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) መታሰቢያ የጥሎ ማለፍ ስፖርታዊ ውድድር በደመቀ ሁኔታ ቀጥሎ ሚያዚያ 23 ቀን 2017 ዓ.ም አዳማ ከተማ በሚገኘው አበበ ቢቂላ ስታዲየም ፍጻሜውን እንደሚያገኝ ተገለጸ፡፡
ከመጋቢት 6 እስከ ሚያዝያ 5 2017 ዓ.ም በተካሄዱ ውድድሮች በእግር ኳስ በ21 ቡድኖች በተደረጉ የጥሎ ማለፍ ውድድሮች አዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባደረጉት ጨዋታ ንግድ ባንክ 2 ለ 0 ሲያሸንፍ፤መከላከያ ኮንስትራክሽን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጫውቶ መከላከያ ኮንስትራክሽን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡ የሁለቱ ጨዋታዎች አሸናፊዎች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመከላከያ ኮንስትራክሽን ለፍጻሜ ለማለፍና ከአዳማ ከተማ አሸናፊ ጋር ለዋንጫ ለመወዳደር ሚያዝያ 20/2017 ዓ.ም ውድድራቸውን እንደሚያካሂዱ የኢሠማኮ የስፖርት ክፍል ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ካሳ ገልጸዋል፡፡
አዳማ ከተማ ላይ አዳማ ውሀና ፍሳሽ፣ወንጂ ስኳር ፋብሪካ፣ አዋሽ መልካ ኬሚካል እና በላይ አክ የተባሉ አራት ቡድኖች የእግር ኳስ ውድድር እያካሄዱ ነው ያሉት አቶ ዮሴፍ ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም አዋሽ መልካ ከበላይ አክ እንዲሁም ወንጂ ስኳር ፋብሪካ ከአዳማ ውሀና ፍሳሽ ይጫወቱና የነሱ አሸናፊ ከአዲስ አበባ ከመጡት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ከመከላከያ ኮንስትራክሽን አሸናፊ ጋር ሚያዚያ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ተጠባቂውን የዋንጫ ጨዋታ ያካሂዳሉ፡፡
በሌላ በኩል በቮሊቦል ወንዶች አዲስ አበባ ውሀና ፍሳሽ ከፋፋ ምግብ አክሲዮን ማህበር ለዋንጫ ሲገናኙ ለደረጃ ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ ድርጅት ጋር ይጫወታሉ፡፡ በሴቶች ቮሊቦል አዲስ አበባ ውሀና ፍሳሽ ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ለዋንጫ ሲጫወቱ ኢትዮ ቴሌኮም ከመከላከያ ኮንስትራክሽን ለደረጃ ይጫወታሉ፡፡
በወንዶች ጠረጴዛ ቴኒስ ኢትዮ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከብርሃንና ሰላም ድርጅት የፍጻሜ ውድድር ሲያካሂድ የአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ ድርጅት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደረጃ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ፡፡ በሴቶች ጠረጴዛ ቴኒስ የአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ ድርጅት እና ኢትዮ ቴሌኮም ለዋንጫ ሲጫወቱ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከብርሃንና ሰላም የደረጃ ውድድር ያካሂዳሉ፡፡ በሌላ በኩል በወንዶች ዳርት ውድድር መከላከያ ኮንስትራክሽን ከኢትዮ ቴሌኮም ለዋንጫ ሲጫወቱ ብርሃንና ሰላም እና ፋፋ ምግብ አክሲዮን ማህበር ለደረጃ ይፎካከራሉ፡፡ በሴቶች ዳርት የአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ ድርጅትና ከብርሃንና ሰላም ለየፍጻሜ ውድድር ሲያካሂዱ ብሔራዊ አልኮልና ኢትዮ ቴሌኮም ለደረጃ እንደሚጫወቱ ከስፖርት ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ሌላው የቤት ውስጥ ውድድር ከረንቡላ ሲሆን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከከብርሃንና ሰላም ለዋንጫ ሲጫወቱ የደረጃው ሶስተኛ ኢትዮ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ድርጅት መሆኑን አረጋግጧል፡፡ በዳማ በሚደረግ ውድድር የአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ ድርጅት ከኢትዮ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ድርጅት ለዋንጫ ሲፎካከሩ ፋፋ ምግብ አክሲዮን ማህበር ከብርሃንና ሰላም ለደረጃ ይጫወታሉ፡፡ በቼዝ በሚደረጉ ውድድሮች ኢትዮ ቴሌኮም ከአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ ድርጅት የፍጻሜ ውድድር እንደሚያደርጉ ለማወቅ ችለናል፡፡
በሁሉም አይነት የቤት ውስጥ ስፖርታዊ ውድድር አይነቶች ለፍጻሜ ለማለፍ የተደረጉት ውድድሮች በሙሉ አዲስ አበባ ውስጥ የተካሄዱ ሲሆን የዋንጫና ለደረጃ የሚካሄዱ ውድድ

25/03/2025

Address

Bole Road
Addis Ababa
3653

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Confederation of Ethiopian Trade Unions/ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Confederation of Ethiopian Trade Unions/ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን:

Share