Liben Abdisa - Lawyer

Liben Abdisa - Lawyer በፍታሐብሄርና ወንጀል ጉዳዬች የማመከር እና የጥብቅና አገልግሎት

የፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች የስራ ዉል የሚቆረጥበት የህግ አግባብ ⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖ የፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች በየቢሮዉ ከፌደራል መንግስቱ ጋር በሚያደርጉት የ...
02/09/2025

የፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች የስራ ዉል የሚቆረጥበት የህግ አግባብ ⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖
የፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች በየቢሮዉ ከፌደራል መንግስቱ ጋር በሚያደርጉት የስራ ቅጥር ዉል አማካኝነት በሚፈጥሩት የቅጥር ግንኙነተት አማካኝነት የሥራ ውል በሕግ የሚቋቋመ ሲሆን ይህ በህግ የሚቋቋም የስራ ዉል የሚቋረጠውም በሕግ መሠረት ነው። የስራ ዉል ሊቋረጥ የሚችልባቸዉን ሁኔታዎች አስመልክቶ በፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 ስር የሥራ ውል የሚቋረጥባቸውን ሁኔታዎችን በዝርዝር ተደንግጎ ይገኛል፡፡
በአዋጁ ስር የስራ ዉል የሚቋረጥባቸዉ የህግ አግባቦች ተብሎ ከተዘረዘሩት ዉስጥ በራስ ፈቃድ የሥራ ውልን ማቋረጥ አንደኛዉ ሲሆን ይህም በአዋጁ በአንቀጽ 135 መሰረት ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በማንኛውም ጊዜ የሁለት ወር ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ሥራውን በፈቃዱ ሊለቅ የሚችል መሆኑን ይደነግጋል፡፡ መስሪያ ቤቱ ሠራተኛውን በቀላሉ ሊተካው የሚችል ከሆነ የሁለት ወሩን ጊዜ ሳይጠብቅ ስንብቱን ሊፈቅድለት ይችላል። ነገር ግን የመንግሥት ሠራተኛው ለሥራው እጅግ አስፈላጊና በቀላሉ ለመተካት የማይቻል ሆኖ ሲገኝ ወደ ፊት ከሚቀጠርበት መስሪያ ቤት ጋር በመስማማት የመልቀቂያ ጥያቄው ሠራተኛው ካመለከተበት ቀን ጀምሮ ከአራት ወር ለማይበልጥ ጊዜ ሊራዘም እንደሚችል ተደንግጓል። የሁለት ወር የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ አገልግሎቱን ያቋረጠ የመንግሥት ሠራተኛ ግዴታውን ባለመወጣቱ ለሚደርሰው ጉዳት እንደተገቢነቱ በፍትሐብሔር እና በወንጀል ሕግ መሠረት ተጠያቂ ይሆናል፡፡
ሌላኛዉ በአዋጁ መሰረት የስራ ዉል የሚቋረጥበት መንገድ በችሎታና ብቃት ማነስ ምክንያት በአሰሪዉ አነሳሽነት የስራ ዉል ሊቆረጥ የሚችል ስለመሆኑ ተደንጎጎ የሚገኝ ሲሆን የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወር በሥራ አፈፃፀም ውጤቱ የችሎታ ማነስ ከታየበት ምክርና ተገቢው የአቅም ማጎልበት የሚሰጠው ሆኖ የመንግሥት ሠራተኛ በተመደበበት ሥራ ላይ የሥራ አፈፃፀም ውጤቱ በበጀት ዓመት ለሁለት ጊዜ ያህል ከመካከለኛ ውጤት በታች ካገኘ በአዋጁ አንቀጽ 137 መሰረት በዕቅድ አፈፃፀም የችሎታ ማነስ ምክንያት ከሥራ የሚሰናበት እና የስራ ዉሉ የሚቋረጥ ይሆናል፡፡
በተጨማሪም ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ከተመደበበት ሥራ ጋር በተያያዘ በብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሂደት በስድስት ወር ለሁለት ጊዜ ያህል ተመዝኖ ከዝቅተኛ ማለፍያ ውጤት በታች
ካገኘ በብቃት ማነስ ምክንያት ከሥራ ይሰናበታል። ነገር ግን የመንግሥት ሠራተኛውን ከሥራ ማሰናበት የሚቻለው እንደ አስፈላጊነቱ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 47 የሥራ አፈፃፀም ምዘና ዓላማ እና አንቀጽ 136 ላይ የጡረታ መብት ተጠብቆ አገልግሎትን ስለማቋረጥ የተደነገገውን በመከተል ይሆናል፡፡
# #የህግ አማካሪ እና ጠበቃ ሊበን አብዲሳ
# #0923279532/ 0911899569

👉በደረቅ ቼክ የወንጀል ክስ የቀረበበት ሰዉ ቼኩን እንደ መያዣነት ነዉ የሰጠሁት በማለት ከወንጀል ተጠያቂነት ለማምለጥ ይችላል?⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖ በሃገራችን በተለያዩ...
30/08/2025

👉በደረቅ ቼክ የወንጀል ክስ የቀረበበት ሰዉ ቼኩን እንደ መያዣነት ነዉ የሰጠሁት በማለት ከወንጀል ተጠያቂነት ለማምለጥ ይችላል?

⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖
በሃገራችን በተለያዩ የንግድ እንቅስቃሴዎች ዉስጥ ቼክ እንደዋስትና ሰነደ በመቀባበል ግብይቶችን መፈጸም የተለመደ ተግባር ነዉ፡፡ በዚህ ረገድ ቼክ ተላላፊ የገንዘብ ሠነድ እንደመሆኑ በዋስትና ሊሰጥ አይቻልም የሚል ድንጋጌም ያሌለ በመሆኑ በመርህ ደረጃ ቼክ ለዋስትና ሊሰጥ ይችላል:: ይሁንና አንድ ሰው ቼክ ጽፌ የሰጠሁት እንዲመነዘር ሳይሆን ካለን የንግድ ግንኙነት የተነሣ ለመተማመኛ/ለመያዣ/ለዋስትና ስለሆነ ቼኩን ስጽፍ ወይም ቼኩ ለክፍያ በቀረበበት ጊዜ በቼክ በማንቀሳቅሰው ሒሳብ ውስጥ በቂ ገንዘብ ባለመገኘቱ በወንጀል ልጠየቅ አይገባም ብሎ የሚከራከር ከሆነ ይህን ማስረዳት የሚችለው በንግድ ሕጉ [አንቀጽ 952] እና በፍትሐ ብሔር ሕጉ [አንቀጽ 2864-2866] መሠረት የተደረገ የመተማመኛ/የዋስትና/የመያዣ ውል በማቅረብ ነው::
ስለሆነም አንድ ሰዉ በቂ ስንቅ ያሌለዉ ቼክ ጽፎ (ደረቅ ቼክ) ለሌላ ሰዉ ሰጥቶ በዚህም የተነሳ የወንጀል ክስ ቢቀረብበተና ቼኩን የሰጠሁት እንዲመነዘር ሳይሆን ካለን የንግድ ግንኙነት የተነሣ ለመተማመኛ/ለመያዣ/ለዋስትና ነዉ የሚል ክርክር የሚያነሳ እንደሆነ በጽሑፍ የተደረገ የመተማመኛ/የዋስትና/የመያዣ ውሉ በማቅረብ ሊያስረዳ የሚገባ ስለመሆኑ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅፅ 25 የሰ/መ/ቁ 161448 ስር አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡

⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖
የህግ አማካሪ እና ጠበቃ ሊበን አብዲሳ
0923279532/ 0911899569

23/08/2025

እዉነት ግን የሰዉ ሚስት ወይም ባል መጋበዝ በህግ ያስቀጣል?
==============================
ከሰሞኑን የሰዉ ሚስት ወይም ባል መጋበዝ በህግ ያስቀጣል በማለት በሶሻል ሚዲያ ሲዘዋወር የነበረዉ ጉዳይ በቡዙ ሰዎች ላይ አግራሞት የፈጠረ እና የህጉን መንፈስ የልጠበቀ አረዳድ የፈጠረ እንደሆነ በዙራዬ ካሉ ወዳጆቼ የተረዳዉት እዉነት ነዉ፡፡ እዉነት ግን የሰዉ ሚስት ወይም ባል መጋበዝ በህግ ያስቀጣል??
ይህን ጉዳይ የሚመለከተዉ የህግ ክፍል በፍትሐ ብሔር ህጋችን ከዉል ዉጪ ኃላፊነትን የሚመለከተዉ የህግ ክፍል አንቀጽ 2050 ስር ተደንግጎ የሚገኝ ሲሆን የህጉ እሳቤና አላማ በሶሻል ሚዲያ እንደተላለፈዉ መጋበዝ አሊያም መገባበዝን ህገወጥ ተግባር ማድረግ አይደለም፡፡ የህጉ ግልጽ ሃሳብ ባለትዳር ከሆነች ወይም ከሆነ ግለሰብ ጋር አላስፈላጊ ግንኙነት እንዳይፈጸም መከላከልን ታሳቢ ያደረገ ድንጋጌ ነዉ፡፡ በህጉ በግልጽ እንደተደነገገዉ አንዲት ሴትን ባሉዋ ነገሩን እንደሚቀወም እያወቀ በቤቱ አስቀምጦ የስተናገደ ወይም የጋበዘ እንደሆነ የህግ ተጠያቂነት የሚያስከትል ስለመሆኑ የሚደነግግ ነዉ፡፡ ይህ ማለት በህዝባዊና ግልጽ በሆኑ ቦታዎች ላይ መገባበዝን የሚከለክል አይደለም፡፡
ስለሆነም ወገን ሳት ሳቀቁ ተገባበዙ😜🥂🥂🥂
የህግ አማካሪ እና ጠበቃ ሊበን አብዲሳ
0923279532/ 0911899569

👉የሽያጭ ዉል በሃገራችን  የፍትሐብሔር ህግ ::::::::::::::::///::::::::///::::::::::::::የሽያጭ ዉል በሃገራችን የፍትሐብሔር ህግ በሻጭና በገዥ መሀከል አንድን ነገር...
11/12/2024

👉የሽያጭ ዉል በሃገራችን የፍትሐብሔር ህግ
::::::::::::::::///::::::::///::::::::::::::

የሽያጭ ዉል በሃገራችን የፍትሐብሔር ህግ በሻጭና በገዥ መሀከል አንድን ነገር አስመልክቶ አንደኛው ወገን የተወሰነ ገንዘብ (price) ለመክፈል ሌላኛው ወገን ደግሞ ዕቃውን ከነ ባለሀብትነቱ ለማስረከብ የሚገቡት ውል ስለመሆኑ ተገልጾ ይገኛል፡፡

ከሽያጭ ውል አይነተኛ ባህሪያት አንዱ ባለሀብትነትን ለገዥ ማስተላለፉ ነው፡፡ ይህም በፍ/ብ/ሕ/ቁ 2281-86 ተመላክቶ ይገኛል፡፡ ይህ የሆነበት ዋነኛ ምክንያትም የሽያጭ ውል አላማ ገዥን ባለቤት ማድረግ ነው፡፡ በመሆኑም ሻጩ ዕቃውን ለገዥ ከማስረከቡ በተጨማሪ ባለቤትነትን ማስተላለፍ አለበት፡፡ ባለቤትነት በዋናነት በሕግ ወይም በውል ሊተላለፍ ይችላል፡፡ ባለቤትነት በሕግ ከሚተላለፍባቸው መንገዶች አንዱ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1161 ላይ የተጠቀሰው የቅን ልቦና ባለይዞታነት (good faith acquisition) መሰረት ነው፡፡ ባለቤትነት በውል ሲተላለፍ የተላለፈለት ወገን ገዥ ከአስተላላፊው ሻጭ ያነሰ መብት ሊኖረው አይችልም፡፡ ይህ ሀሳብ በላቲት nemo dat qua non habet የሚባለው ሲሆን ትርጉሙ ማንም የሌለውን መብት ( ባለቤትነት) ሊያስተላልፍ አይችልም ነው፡፡ በመሆኑም ሻጭ መብቱን ከማስተላለፉ በፊት በርግጥ የባለቤትነት መብት ያለው መሆን መቻል ይኖርበታል፡፡

# # ሊበን አብዲሳ ጠበቃ እና የህግ አማካሪ
# # 0923279532
# # 0715541919

09/12/2024

👉👉የሁከት ይወገድ ክስ መሠረቱ

የሁከት ይወገድልኝ ክስ (Possessory Action) አንድ ሰው በይዞታው ሥር ወይም በጥበቃው ሥር ባለው ንብረት ላይ የግፊያ ወይም የንጥቂያ ተግባር ሲፈጸም ይህ ተግባር እንዲቆም ወይም የተነጠቀው ንብረት እንዲመለስ ፍርድ ቤት እንዲያዝለት ሲጠይቅ ነው፡፡

ከዚህ የሕጉ አገባብ ላይ ለሁከት ይወገድልኝ ክስ መሠረት የሆኑትን ዋና ዋና ነጥቦች መገንዘብ ይቻላል፡፡ እነዚህም
1ኛ/ አንድ ሰው የሁከት ይወገድልኝ ክስ ማቅረብ የሚችለው በይዞታው ሥር ባለ ንብረት ወይም መብት ላይ የግፊያ ወይም የንጥቂያ ተግባር የተፈጸመበት ባለይዞታ ሲሆን ነው፡፡
2ተኛ የሁከት ይወገድን ክስ ማቅረብ የሚችለው ባለይዞታ ብቻ ሳይሆን የሁከት ተግባር የተፈጸመበት ጠባቂም (holder) ጭምር ሊሆን ይችላል፡:

# # ሊበን አብዲሳ ጠበቃ እና የህግ አማካሪ
# # 0923279532
# # 0715541919

በፍታሐብሄርና ወንጀል ጉዳዬች የማመከር እና የጥብቅና አገልግሎት

👉🏻 ደላላነት በሀገራችን ህግ           👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇በተለምዶ በሀገራችን የደላላነት ስራ ምንም አይነት ፍቃድ ሳይኖራቸዉ የሚሰሩት እና መተዳደሪያቸዉም ጭምር ሆኖ መመልከት የተለመደ ...
29/11/2024

👉🏻 ደላላነት በሀገራችን ህግ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
በተለምዶ በሀገራችን የደላላነት ስራ ምንም አይነት ፍቃድ ሳይኖራቸዉ የሚሰሩት እና መተዳደሪያቸዉም ጭምር ሆኖ መመልከት የተለመደ ነዉ፡፡
ይሁን እንጂ ይሄ ድርጊት የህግ ቅቡልነት ያሌለዉ መሆኑን ከሃገራችን የንግድ ህግ አንቀጽ 5(34) ስር በተደነገገዉ አግባብ ማንኛዉም የንግድ ወኪል፤ የኮሚሽን ወኪል፤ የንግድ ደላላ፤ የአክሲዮን ደላላ በመሆን ስራ የሚሰሩ፤ ማንኛዉንም አይነት የሰዎችን አገናኝነት ስራ የሚሰሩ በንግድ ህጋችነ መሰረት ነጋዴ ተብሎ የሚቆጠሩ መሆኑ ተደንግጎል ይሄም ማንኛዉም እንዲህ ያሉትን ስራ ሚሰራ ሰዉ የንግድ ፍቃድ ሊኖረዉ የሚገባ ስለመሆኑ ያስገነዝበናል፡፡
በዚህ የተያያዘ የደላላነት ንግድ ፍቃድ ሳይኖረዉ የደላላነት ስራ ሲሰራ የነበረ ሰዉ ለሰራዉት የደላላነት ስራ ክፍያ(አበል) ይከፈለኝ ለማለት የማይችል ስለመሆኑ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅጽ 25 በሰ/መ/ቁ 204199 አስገዳጅ ህግ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡

👉👉ሊበን አብዲሳ ጠበቃ እና የህግ አማካሪ👈👈
# # 0923279532
# # 0715541919

👉👉

ሊበን አብዲሳ በፍትሐብሄር እና ወንጃል ጉዳዮች የህግ አማካሪ እና ጠበቃ # 0923279532 # 0715541919 በዚህ ቻናል የተለያዩ ህግ ነክ የሆኑ ሰነዶች ፡ አዳዲስ እና ነባር ኮዶች : የሰበር ዉሳኔዎች ፡ የ....

25/11/2024

መሰየም የሚለው ቃል ቀጥተኛ ትርጉም ስም መስጠት ወይም ስም ማውጣት መሆኑን በተለያዩ መዝገበ ቃላት እናገኘዋለን፡፡ ይህ ግን ሕጉ ማለት የፈለገውን በቀላሉ ለመረዳት የሚያስችል ላይሆን ይችላል፡፡ ከዚህ ይልቅ የወንጀል ሕጉ በእንግሊዝኛ ቅጂው የተጠቀመው “Reinstatement” የሚለው ቃል የተሻለ አመላካች ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 232(1) መሰየም የተወሰነበትን ቅጣት የፈፀመ ወይም ቅጣቱ በይርጋ ወይም በይቅርታ የቀረለት ወይም ፍርዱ ወይም የቅጣቱ አፈፃፀም ያታገደለት ወይም በአመክሮ የተለቀቀ ማንኛውም ጥፋተኛ በሕጉ የተቀመጡትን ግዴታዎች በመፈፀም ከመቀጣቱ በፊት የነበረውን ንፁህ ስም እንዲመለስለትና ፍርድ እንዲሰረዝለት የሚጠይቅበት ሂደት ስለመሆኑ ይገልፃል፡፡

 #ዊዝሆልዲንግ ታክስ⤵️ዊዝሆልዲንግ ታክስ ከተሰብሳቢ ሂሳብ ላይ ሳይሆን ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ተቀንሶ የሚያዝ ታክስ አይነት ነው፡፡  በህጉ በተመለከቱት ሂሳቦች ላይ አንድ ሰው ግብይት በማካሄ...
28/04/2024

#ዊዝሆልዲንግ ታክስ⤵️

ዊዝሆልዲንግ ታክስ ከተሰብሳቢ ሂሳብ ላይ ሳይሆን ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ተቀንሶ የሚያዝ ታክስ አይነት ነው፡፡ በህጉ በተመለከቱት ሂሳቦች ላይ አንድ ሰው ግብይት በማካሄድ ሂሳብ ሲከፍል ከሚከፍለው ክፍያ ላይ ቀንሶ በመያዝ የሚከፈል ታክስ ነው፡፡ ዊዝ ሆልዲንግታክስ ከራስ ገቢ ላይ ግብር ቀንሶ መያዝንም ይጨምራል፡፡ በዚህም መሰረት ገቢውን የሚያገኘውም ሆነ ግብሩን ቀንሶ በመያዝ የሚከፍለው ራሱ ገቢውን ያገኘው ሰው ነው፡፡
ከተካፋይ ሂሳብ ላይ ግብር ቀንሰው እንዲያስቀሩ ሃላፊነት የተሰጣቸው አካላት
በግዥ ወቅት ከሚፈጽሙት ክፍያ ላይ ግብር ቀንሰው እንዲያስቀሩ ግዴታ የተጣለባቸው ሰዎች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው፦

▪ በህግ የሰውነት መብት የተሰጣቸው ድርጅቶች፡- የአክሲዮን ማህበር፣ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ የሽርክና ማህበር፣ የህብረት ስራ ማህበር… ወዘተ፣
▪ የመንግስት መ/ቤቶች፡- በፌደራል እና በክልል የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ለመንግስት መ/ቤቶች በተሰጠው ትርጉም ውስጥ የሚካተቱ ወይም በተቋቋመበት ህግ የመንግስት መ/ቤት የተባሉ የፌደራል፣ የክልል፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት መ/ቤቶች፣
▪ ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች፡- ለትርፍ ላልሆነ ለተለያዩ ዓላዎች የተቋቋሙ ማህበራትና የሃይማት ድርጅቶች፤
▪ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፡- በሲቪክ ማህበራት አዋጅ መሰረት የተቋቋሙ ‹‹የኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች›› ወይም ‹‹የኢትዮጵያ ማህበሮች›› ወይም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ በውጭ አገር የተቋቋሙ ተመሳሳይ ድርጅቶች፤
▪ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት በምርት ገበያው አማካማኝት ከሚከናወን ግብይት ጋር በተያያዘ ገዥውን በመወከል የሚፈፅመው ግብይት፤
▪ ከተከፋይ ሂሳብ ላይ የንግድ ትርፍ ግብር ቀንሰው ገቢ እንዲያደርጉ ሃላፊነት የተሰጣቸው ግለሰብ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ባለፉት ሶስት ተከታታይ ዓመታት በአማካይ አስር ሚሊዮንና ከዚያ በላይ ጠቅላላ ገቢ ያስመዘገቡ ግለሰብ ግብር ከፋዮች፤
▪ ቀጥሎ በተመለከቱት የንግድ ስራ ዘርፎች የተሰማሩ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ሽያጫቸው ከግምት ውስጥ ሳይገባ ግብር ቀንሰው የማስቀረት ግዴታ አለባቸው፡-
➢ ማንኛውም ባለ ኮከብ ሆቴል ወይም ማንኛውም ሪዞርት፤
➢ ከ1 እስከ 4 ደረጃ ያላቸው ስራ ተቋራጮች፤
➢ ማንኛውም ሪል ስቴት አልሚ፤
➢ የምግብ አምራች ኢንዲስትሪዎች ፤
➢ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ግዢ የሚፈፅም ማንኛውም ግለሰብ ግብር ከፋይ በምርት ገበያው በኩል ላደረገው ግብይት ብቻ፤
➢ ሆስፒታሎች እና በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መስፈርት መሰረት ከፍተኛ እና ከዚህ በላይ ያላቸው ክሊኒኮች ፤
➢ ዩኒቨርሲቲዎች እና ኮሌጅ እንዲሁም
➢ ከአምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት በመረከብ የሚያከፋፍል ማንኝውም ግለሰብ ግብር ከፋይ፡፡
ግብር ቀንሶ የመያዝ ግዴታ የማይመለከታቸው አካላት ፡-
የሚከተሉት በግዢ ወቅት ከሚፈጽሙት ክፍያ ላይ ግብር ቀንሶ የማስቀረት ግዴታ የለባቸውም፡፡
❖ ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች፤
❖ ላኪዎች/ ወደ ውጭ ለሚልኳቸው ምርቶች በግብዓትነት ለሚያገለግሉ እቃዎች ብቻ/ በዲፕሎማቲክ እና አለም አቀፍ ስምምነት መሰረት የተቋቋሙ ድርጅቶች፣ የውጭ ዲፕሎማቲክ ኮንሱላር ሚሲዮኖች፣ ኤምባሲዎች፣ የተባበሩት መንስታት ድርጅት አካላት እና የዲፕሎማቲክ መብት ያላቸው ተመሳሳይ አካላት፣
❖ የገቢዎች ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ ቅድመ ግብር የመያዝ ግዴታ ከተጣለባቸው ግለሰብ ግብር ከፋዮች ውጪ ያሉ ግለሰብ ግብር ከፋዮች፡፡

#ሊበን አብዲሳ የህግ አማካሪ እና ጠበቃ
#0923279532
://t.me/libenlawyer

🛑 source #የሕግ አገልግሎት

Address

Addis Ababa

Telephone

+251923279532

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Liben Abdisa - Lawyer posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Liben Abdisa - Lawyer:

Share