የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን We are the only Foreign Employment Associations Federation in Ethiopia

23/01/2017 ዜና EOEAF የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን የዜጎችን መብት ለማስከበር ከኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ጋር የጋራ የመግባቢ...
03/10/2024

23/01/2017
ዜና EOEAF
የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን የዜጎችን መብት ለማስከበር ከኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡

የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን በውጭ ሀገር በስራ የሚሰማሩ ዜጎችን መብት እና ደህንነት ለማስጠበቅ ከዚህ ቀደም በጋራ አብሮ ለመስራት በመርህ ደረጃ ንግግር ሲያደርግ የነበረ ሲሆን ዕለተ ሀሙስ መስከረም 2017 በኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ከሁለቱም በኩል የሥራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የአለም አቀፉ የሥራ ድርጅት ተወካይ፣ የተለያዩ የሚድያ ተቋማት እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡

የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪዎች ፌዴሬሽን ፕሬዝደንት አቶ ነቢል መሀመድ በመክፈቻ ንግግራቸው ፌዴሬሽኑ በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት በስራ የሚሰማሩ ዜጎች መብት፣ ክብር እና ደህንነት እንዲጠበቅ ለኤጀንሲዎች ከመንግስትና ከአለም አቀፉ የሥራ ድርጅት (ILO) ጋር በመተባበር በርካታ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መሰጠታቸውን ጠቅሰው በተለይ ፌዴሬሽኑ ከእነኝሁ የባለድርሻ አካላት ጋር የስነምግባር ደንብ አዘጋጅቶ እና አፀድቆ ኤጀንሲዎች ህግን፣ ዘርፉን በተመለከተ የወጣውን አዋጅ እና አለም አቀፍ መርሆዎችን በጠበቀ መልኩ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አስገንዝበዋል፡፡ ፕሬዝደንቱ አክለውም ፌዴሬሽኑ በዋናነት የአባላቶቹን መብት ከማስከበር ባሻገር የዜጎች መብት፣ ጥቅም እና ደህንነት እንዲከበር የሚሰራ መሆኑን ጠቅሰው ከኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ጋር በዛሬው ዕለት የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድም የዜጎችን መብት በማስከበር ረገድ ጉልህ ሚና የሚጫወት መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝደንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ኮንፌዴሬሽኑ ለዜጎች የሰብዓዊ መብት መከበር ከሚሰራ ከየትኛውም ተቋም ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰው ከኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች ፌዴሬሽን ጋር በጋራ ለመስራት በርካታ ጥረት ሲደረግ የነበረ መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ አክለውም ፕሬዝዳንቱ ይህ የመግባቢያ ሰነድ ወደ ትግበራ ሲገባ በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት የሚሰማሩ ዜጎች ከምልመላ ጀምሮ እስከሚሄዱበት የመዳረሻ ሀገራት እና ቆይታቸው ላይ በጋራ በሚመሰረተው የቅጥር እና የምልመላ አማካሪ ኮሚቴ (Migrant Workers Recruitment Advisory Committee) አማካኝነት መረጃዎችን በመሰብሰብ እና ልውውጥ በማድረግ የዜጎችን መብት ለማስከበር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልፀዋል፡፡ ፕሬዝደንቱ ከኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ጋር በጋራ መስራታቸው በርካታ ዜጎች ህጋዊ በሆነ መንገድ እንዲሰማሩ ከማገዝ በተጨማሪ ዜጎች ላይ የተለያዩ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንዳይፈፀምባቸው መረጃዎችን ለመለዋወጥ የሚያስችል መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

የመግባቢያ ሰንዱ ላይ በተቀመጠው መሰረት ጥምር ኮሚቴ በመመስረት እና የጋራ አክሽን ፕላን በማውጣት ወደ ውጭ ሀገር በሥራ የሚሰማሩ ዜጎችን መብት ለማስከበር በርካታ ስራዎች እንደሚሰራ ይጠበቃል፡፡

ዜና EOEAFፌዴሬሽኑ ዘለቄታዊ የገቢ አቅምን ለመፍጠር ያለመ ስትራቴጅ ዕቅድ ለማዘጋጀት ከባለሙያ ጋር ይፋዊ ትውውቅ አደረገ::የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን ...
24/07/2024

ዜና EOEAF

ፌዴሬሽኑ ዘለቄታዊ የገቢ አቅምን ለመፍጠር ያለመ ስትራቴጅ ዕቅድ ለማዘጋጀት ከባለሙያ ጋር ይፋዊ ትውውቅ አደረገ::

የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን በጽ/ቤቱ በአለም አቀፉ የስራ ድርጅት (ILO) የጄ ኤል ኤም ፒ ፕሮጀክት ድጋፍ አማካኝነት የፌዴሬሽኑን (Sustainable Income Generation Strategy Plan) ጥናታዊ ሰነድ ከሚያዘጋጀው ባለሙያ አቶ ግርማ ጋር ይፋዊ ትውውቅ በማከናወን ጥናቱን ለመጀመር የሚያስችል ውይይት ተደርጓል::

በፌዴሬሽኑ በኩል አስተያየታቸውን የሠጡት የጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ረመዳን አሸናፊ ፌዴሬሽኑ በጥናቱ ሂደት ዙሪያ የሚያስፈልጉ ማንኛውን ጠቃሚ ሰነዶች ለባለሙያው ለማቅረብ እና ጥናቱ ተግባራዊ እና ችግር ፈቺ ሆኖ እንዲከናወን ለማድረግ ፌዴሬሽኑ በሙሉ አቅም ተሳታፊ ሆኖ እንደሚቀጥል ያለዉን ቁርጠኝነት አስረድተዋል::

በ ILO JLMP ፕሮጀክት በኩል ወ/ሮ ኡቼ እና አቶ ሰለሞን በበኩላቸው ውጤታማ ጥናታዊ ሰነድ እንዲዘጋጅ ሱፐርቫይዝ ከማድረግ ባለፈ ጥናቱ እንዲሳካ ሙሉ ድጋፋቸው እንደማይለይ ገልፀዋል::

ባለሙያው አቶ ግርማ በበኩላቸው እዉቀታቸውንና በርካታ ልምዳቸውን በመጠቀም ከሰነድነቱ አልፎ ተግባራዊ የሚሆን ለፌዴሬሽኑን ዘለቄታዊ አቅም የሚፈጥር ጥናት እንደሚሰሩ ገልፀዋል::

ዜና EOEAF የትግራይ ክልል የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ፈተናዎች እና መልካም ዕድሎችበትግራይ ክልል መቀለ ከተማ የትግራይ ክልል የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን አስመልክቶ የፌዴራል ሥ/ክ/ሚኒስቴር...
21/06/2024

ዜና EOEAF

የትግራይ ክልል የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ፈተናዎች እና መልካም ዕድሎች

በትግራይ ክልል መቀለ ከተማ የትግራይ ክልል የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን አስመልክቶ የፌዴራል ሥ/ክ/ሚኒስቴር፣ የ አይ ኤል ኦ (ILO) እና የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ተወካዮች በተገኙበት ወርሀ ሚያዝያ ላይ በክልሉ የተሰጠ የአቅም ግንባታ ስልጠና ውጤቶችን ዙሪያ ግምገማ ተደርጓል፡፡
ከዚህ ቀደም በወርሀ ሚያዝያ በትግራይ ክልል ውስጥ ከተለያዩ ዘጠኝ ወረዳዎች ለተውጣጡ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት እና ስራ ዕድል ፈጠራ ቢሮዎችና በክልሉ ለሚገኙ በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ለተሰማሩ ኤጀንሲዎች የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ተወካይ በተገኘበት ህገወጥ ስደትን ለመከላከልና ህጋዊዩን የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን ለማጠናከር ያለመ ስልጠና በሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር እና አይ ኤል ኦ አስተባባሪነት የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

ዕለተ ሀሙስ እና አርብ በመቀሌ ከተማ በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ከዚህ በፊት ስልጠናው ላይ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ ወርሀ ሚያዝያ ላይ የተሰጠው የ አቅም ግንባታ ስልጠና የአመጣቸው ውጤቶች ላይ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የቆየ ግምገማ ተደርጓል፡፡ በዚህ ግምገማ የክልሉ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ባለ ሰባት ገፅ የግምገማ ሪፖርት ያቀረበ ሲሆን ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ በቀጠይ የአጭር፣ የመካከለኛ እና የረጂም ጊዜ ዕቅድ ተደረገው መሰራት ባለባቸው አንኳር ነጥቦች ላይ ሁሉም የውይይቱ ተሳታፊዎች ሀሳብ ሰጥተዋል፡፡

እንደ አጠቃላይ በወርሀ ሚያዝያ የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና በክልሉ ስለውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት መነቃቃት የፈጠረ ቢሆንም ትግራይ ክልል በነበረው አውዳሚ ጦርነት ምክንያት በርካታ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ወደ ሥራ አለመግባታቸው የተገለፀ ሲሆን በርካታ ቁጥር ያለው ዜጋ ሰልጥኖ በውጭ ሀገር በሥራ ለመሰማራት ፍላጎቱ ያላቸው ወጣቶች ላይ እንቅፋት እንደሆነባቸው ተብራርቷል፡፡ ሰልጥነው የሙያ ብቃት ፈተና ወስደው የጨረሱ ወጣቶችም ቢሆኑ በክልሉ የLMIS ሲስተም አገልግሎት ባለመጀመሩና ኦንላይን ባለመሆኑ ምክንያት ለበርካታ እንግልት እየተዳረጉ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ በዚህም ሳቢያ በክልሉ ፍቃድ ወስደው እየሰሩ የሚገኙ በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት የተሰማሩ ኤጀንሲዎችም ቢሆኑ በተለያዩ ተጨማሪ ምክንያቶች ለከፍተኛ ኪሳራ በመዳረጋቸው ቢሯቸውን እየዘጉ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
በመጨረሻም በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዙሪያ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር የተያያዙ የኤል ኤም አይ ኤስ እንዲሁም የምደባ ስነ ስርዓቱ ላይ የሚታዩ ክፍተቶች ላይ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥባቸው ሀሳብ የተሰጠብት ጉዳይ ሲሆን በነዚህና ትግራይ ክልል በሚያስፈልገው የተለያየ የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፎች ላይ ከፌዴራል የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ቢሮ ጀምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የትኩረት አቅጣጫ አድረገው መስራት ያለባቸው ስራዎች ላይ ስራዎችን በመከፋፈል የግምገማ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

በኢትዮጵያ እና በኩዌት መንግስት በኩል ኢትዮጵያዉያን ሰራተኞችን ወደ ኩየት ለመላክ ግንቦት ሰኞ 19 2016 ዓ.ም የተደረሰዉን ስምምነት ተከትሎ የኢትዮጵያ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገናኝ ...
01/06/2024

በኢትዮጵያ እና በኩዌት መንግስት በኩል ኢትዮጵያዉያን ሰራተኞችን ወደ ኩየት ለመላክ ግንቦት ሰኞ 19 2016 ዓ.ም የተደረሰዉን ስምምነት ተከትሎ የኢትዮጵያ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን በጽ/ቤቱ ከኩዌት አቻ ማህበር ጋር የዜጎችን መብት ; ክብር እና ደህንነት ባስጠበቀ መልኩ እንዲሁም በዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት የተሰማሩ ኤጀንሲዎችን ጥቅም ባስከበረ መልኩ የሁለትዮሽ ስምምነት አፅድቀዋል::

ዝርዝር መረጃዎችን በተመለከተ ለሁሉም በዉጭ ሀገር ስራ ለተሰማሩ ኤጀንሲዎች በቅርቡ በተከታታይ የምንለቅ ይሆናል::

ፌዴሬሽኑ

https://youtu.be/dP9ZL8uid4E?si=uPLN5Ab7T17INSu-
02/01/2024

https://youtu.be/dP9ZL8uid4E?si=uPLN5Ab7T17INSu-

የፌዴሬሽኑ ልዑካን ቡድን በሪያድ የዓለም አቀፍ የሰው ሀይል አገልግሎት ኤክስፖ ላይ በነበረው የአራት ቀን ቆይታከመንግስት ጋር ኢትይዮጵያ ያላትን እምቅ የሰው ሀይል በማስተዋወቅ ረገ.....

በሳዑዲ አረቢያ ዋና ከተማ ሪያድ እየተካሄደ ባለው የሰው ሀይል እና ሥራ አገልግሎት ኤግዚቢሽን ጎንለጎን የፓናል ውይይት ተካሄደ:: በሰው ሀይል አቅርቦት ዘርፍ የሀገራት ግንኙነት እና የኢትዮ...
27/12/2023

በሳዑዲ አረቢያ ዋና ከተማ ሪያድ እየተካሄደ ባለው የሰው ሀይል እና ሥራ አገልግሎት ኤግዚቢሽን ጎንለጎን የፓናል ውይይት ተካሄደ::

በሰው ሀይል አቅርቦት ዘርፍ የሀገራት ግንኙነት እና የኢትዮጵያ ተሞክሮ በሚል ርዕስ በሳዑዲ አረቢያ ዋና ከተማ ሪያድ እየተካሄደ ባለው 4ተኛ ዙር የፓናል ውይይት በሳዑዲ አረቢያ የኢትይዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን ክቡር አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ፣ የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ነቢል ሙሀመድ፣ በሳዑዲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የቆንጽላ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ኡመር አሕመድ፣ በሥራና ክህሎት ሚንስቴር የገቢያ እና መረጃ ሥርዓት ቁጥጥር ምክትል ኃላፊ አቶ ሳልሕ እና በሳዑዲ አረቢያ በሰው ሀይል ዘርፍ ኢንቨስተር የሆኑት ዶር ሁሙድ አልኡተይቢ በተገኙበት የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡
በዚህ የፓናል ውይይት በሰው ሀይል ዘርፍ ዙሪያ የኢትዮጵያ እና ሳዑዲ አረቢያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ምን እንደሚመስል እና በቀጣይ እየተስተዋሉ ያሉ ተግዳሮቶችን በመቀነስ ወደተሻለ ደረጃ ከፍ እንዲል ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ምክረ ሀሳቦች ተሰንዝረዋል፡፡ በፓናል ውይይቱ ላይ ተሳታፊ የሆኑት እና የመጀመሪያውን እድል የወሰዱት ክቡር አምባሳደር ሌንጮ ባቲ የኢትዮጵያ እና የሳዑዲ አረቢያ ግንኙነት ቀደምት መሆኑን በመጥቀስ እንዲሁም ሁለቱ ሀገራቶች ካላቸው ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ፣ ቅርበት እምነትና የባህል መመሳል አንፃር ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ከኢትዮጵያ ወደ ሳዑዲ አረቢያ በመምጣት በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የሚሰማሩብትና የሥራ እድል የሚፈጠርበት ሁኔታ እየተጠናከረ መምጣቱን አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ነቢል ሙሀመድ በብኩላቸው የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን በሥሩ ከሰባት መቶ በላይ ኤጀንሲዎችን ያቀፈና በውጭ ሀገር ሥራ መሰማራት ለሚፈልጉ ዜጎች የመንግስትን አዋጅ እንዲሁም ህግና ደንቦችን መሰረት ባደረገ መልኩ በርካታ የሥራ እድሎች በሳዑዲ አረቢያ እንዲፈጠር እንደፌዴሬሽን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ በሥሩ ላሉ በርካታ ኤጀንሲዎች የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ከሥራ እና ክህሎት ሚንስቴር እንዲሁም አለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመሆን በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዘርፍ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ጥረት እየተደረገ መሆኑን በተጨማሪ አስገንዝበዋል፡፡
በዚሁ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዘርፍ ከኢትዮጵያ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሰራተኞችን በመላክ ዙሪያ እየተስተዋሉ ያሉ ተግዳሮቶችን መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ በኢትዮጵያ የሳዑዲ ኢምባሲ የቆንጽላ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ኡመር አሕመድ ሀገራት የተስማሙበትን የሁለትዮሽ ስምምነት አክብሮ መስራት እንደሚያስፈልግ እና በሳዑዲ አረቢያ በኩልም ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ከመኖሪያ እና የምግብ አቅርቦትና ሌሎች ጉዳዮች ጋር ተያይዞ መብታቸው እንዲከበር የሚመለከተው አካል ትኩረት መስጠት እንዳለበት አፅንዖት ሰጥተውበታል፡፡ በሥራና ክህሎት ሚንስቴር የገቢያ እና መረጃ ሥርዓት ቁጥጥር ምክትል ኃላፊ አቶ ሳልሕ በበኩሉ የሥራ እና ክህሎት ሚንስቴር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባካሄዳቸው የሲስተም እና ቴክኖሎጂን የተደገፈ አሰራር አብዛኞቹ የሥራ ውሎች እና ተጨማሪ ዶክመንቶች ደረጃ በደረጃ የሚፀድቁበት እና ትክክለኛነታቸው የሚረጋገጡበት አስፈላጊ ሂደቶችን የሚያልፉ ስለሆነ ፎርጅድ የሆኑ ዶክመንቶች የማይጫኑበት ሁኔታ መፈጠሩን እና በፊት ከነበረው አሰራር የተሻለ አሰራር እንደተገነባ አስረድተዋል፡፡
በሰው ሀይል ዘርፍ ኢንቨስተር የሆኑት ዶክተር ሁሙድ ኡተይቢ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በሰው ሀይል አቅርቦት በቤት ሰራተኝነት ከሚመጡ ኢትዮጵያዊ ዜጎች በተጨማሪ ለሌሎች ሙያዎች ጭምር ትኩረት በመስጠት እየሰሩ እንዳሉ እና ኢትዮጵያ በመጣባቸው ጊዜያቶችም ላይ ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንግዳ ተቀባይ እና ታታሪ ለመሆናቸው ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
የተለያዩ ገንቢ ሀሳቦች የተነሱበት ይህ መድረክ በኤክስፖ አዘጋጆች አማካኝነት ለፓናል ውይይት ተሳታፊዎች ሽልማት በማበርከት የተጠናቀቀ ሲሆን በመጨረሻም የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ልዑካን ቡድን እንዲሁም ከሥራ እና ክህሎት የመጡ የቴክኒካል ቡድን አባላት ፓናል ውይይቱ እንደተጠናቀቀ ክቡር አምባሳደር ሌንጮ ባቲ በሳዑዲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ቅጥር ግቢ በጠሩት የራት ግብዣ ተደርጎላቸዋል፡፡
እንደ አጠቃላይ ሀሳባቸውን የሰጡት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ነቢል ሙሀመድ በሳዑዲ የተደረገው የሰው ሀይል አቅርቦት ላይ ያተኮረው ይህ ኤግዚቢሽን ዘርፉ በደንብ ከተሰራበት የሀገርን ገፅታ ከመቀየሩ በላይ በውጭ ምንዛሬ ረገድ ለሀገር ከፍተኛ አስተዋፅዖ እንዳለው ጠቅሰው ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሰራተኞችን ወደ ሳዑዲ በመላክ ከሚገኘው የኮሚሽን መጠን ጋር ተያይዞ በዝቅተኛ ዋጋ የሚሰሩ በርካታ ኤጀንሲዎች መኖራቸውን በኤግዚቢሽን መድረኩ ተሳታፊ ከነበሩ የተለያዩ የሳዑዲ ወኪል ኤጀንሲዎች መረዳት የተቻለ መሆኑን እና በዚህ ረገድ ከመንግስት ጋር እጅና ጓንት በመሆኑ ይህን ሀገርን የሚጎዳ ድርጊት ለመታገል በጋራ መሰራት እንዳለበት ገልፀዋል፡፡

ዜና EOEAF የፌዴሬሽኑን ድህረገፅ እና የሞባይል መተግበሪያ በአዲስ መልኩ ለማበልፀግ የሚያስችል ስምምነት ከሄክስ ላብ ጋር ተደረገ፡፡ የኢትዮጵያ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች...
09/11/2023

ዜና EOEAF
የፌዴሬሽኑን ድህረገፅ እና የሞባይል መተግበሪያ በአዲስ መልኩ ለማበልፀግ የሚያስችል ስምምነት ከሄክስ ላብ ጋር ተደረገ፡፡

የኢትዮጵያ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ስራ አስኪያጅ አቶ ረመዳን አሸናፊና የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ አቶ አሕመድ አዲሴ በተገኙበት በሶፍትዌር ቴክኖሎጂ፣ በድህረገፅና ሲስተም ማበልፀግ ዘርፍ ከሚታወቀዉና በርካታ የፈጠራ ስራዎችን ከሰራው የሄክስ ላብ መስራች እና ስራ አስፈፃሚ ኢዘዲን ካሚልና የስራ አጋሮቹ ጋር በፌዴሬሽን ጽ/ቤት በመወያየት የፌዴሬሽኑን ድህረገፅ በአዲስ መልኩ የተለያዩ መረጃዎችን በማካተት ለማበልፀግ ስምምነት ላይ ተደርሷል::
ስምምነቱ ከድህረገፁ በተጨማሪ የፌዴሬሽኑን ደረጃ ከፍ የሚያደርግ በውጭ ሀገር የሚሰማሩ ዜጎች በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ቅድመ ጉዞ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ “የቅድመ ጉዞ ስንቅ” የሚል ሰነድ እንዲሁም የአባላቱ ኤጀንሲዎችን ስም ዝርዝር ያካተተና ስለፌዴሬሽኑ በቂ መረጃዎችን የሚሰጥ የሞባይል መተግበሪያን ማበልፀግንም ያካትታል፡፡
በድህረገፁም ሆነ በሞባይል መተግበሪያው ውስጥ ሌላው የሚካተተው ጉዳይ ማንኛውም ህጋዊ ኤጀንሲ በፌዴሬሽኑ የታቀፉ ሶስቱ ማህበራት በአንዳቸው ስር እንደየፍላጎታቸው አባል ለመሆን መመዝገብ የሚችሉበት መድረክ ሲሆን ከዚህ ባለፈም በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዜጎች ፌዴሬሽኑ ስለሚሰጣቸው አገልግሎቶች በቀጥታ መልዕክት መፃፍ እና ጥያቄዎችን ማቅረብም ይችላሉ፡፡
ከሥምምነቱ ባሻገር የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት ዘርፍን ማዘመንና በቴክኖሎጅ የተደገፈ ማድረግ የበርካታ አባላት ኤጀንሲዎች ጥያቄም ከመሆኑ በላይ ኋላቀር አሰራርን የሚያስቀርና የዜጎችንም ሆነ የአባላትን ጥቅም የሚያስጠብቅ ስለሆነ በጋራ ስራዎችን ለመስራት የሚስችል የጋራ ስምምነት ለመፈራረም አጭር የጊዜ ገደብ ተቀምጧል::

https://youtu.be/_TS2Zyb61WQ?si=4n3mVLhPVOaotXpC
31/10/2023

https://youtu.be/_TS2Zyb61WQ?si=4n3mVLhPVOaotXpC

የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ወደ ዓረብ ሀገራት በተለያዩ ሙያዎች ሴቶችን ለሥራ የሚያሰማሩ ኤጀንሲዎች ሶስት ማህበራት ውህደት ነው፡፡

16/02/16 ዜና EOEAF የኢትዮጵያ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገናኝ  ኤጀንሲዎች ፌዴሬሽን እና የፍላይ ናስ አየር መንገድ የስራ ሀላፊዎች ዉይይት የኢትዮጵያ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገ...
27/10/2023

16/02/16

ዜና EOEAF

የኢትዮጵያ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች ፌዴሬሽን እና የፍላይ ናስ አየር መንገድ የስራ ሀላፊዎች ዉይይት

የኢትዮጵያ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሰሪ ፌዴሬሽን ስራ አስኪያጅ ፍላይ ናስ ከተባለ የሳዑዲ አየር መንገድ ጋር በጋራ ለመሥራት በጽ/ቤቱ ከአየር መንገዱ የስራ ሀላፊዎች ጋር ተወያይቷል:: ውይይቱን የከፈቱት የፌዴሬሽኑ ሥራ አስኪያጅ አቶ ረመዳን አሸናፊ እንኳን ደህና መጣችሁ ገለፃ ካደረጉ በኋላ ፌዴሬሽኑ ስለሚሰራቸው ሥራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮች ያነሱ ሲሆን ፍላይ ናስን ወክለው የተገኙት የፍላይ ናስ ዋና የፋይናንስ ኦፊሰር ስቴፋን ማጊራ እንዲሁም የፍላይ ናስ የአፍሪካ ተወካይ ሙሀመድ ሀሰን በበኩላቸው ከፌዴሬሽኑ ጋራ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ለመወያየት በመገኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
በውይይቱ የፍላይ ናስ የኢትዮጵያ ተወካይ የሆኑት አቶ ካሳሁን እና ወ/ሮ ሁስኒያም የተገኙ ሲሆን የፍላይ ናስ ዋና የፋይናንስ ኦፊሰር የሆኑት ስቴፋን ማጊራ አየር መንገዱ በመካከለኛዉ ምስራቅ ዝቅተኛ የትኬት ክፍያን የሚያስከፍልና ጥራት ያለዉ አገልግሎት አቅራቢ መሆኑን ጠቅሰው ከፌዴሬሽኑ ጋር በጋራ ለመስራት ሲያስቡ ክፍያን እና ጥራትን ባመጣጠነ መልኩ የሚከናወን መሆኑን ገልፀዋል:: የፍላይ ናስ የአፍሪካ ተወካይ ሙሀመድ ሀሰንም በበኩላቸው ከፌዴሬሽኑ ጋር በጋራ ለመስራት እና ለበርካታ ኤጀንሲዎች አገልግሎቱን ለማድረስ ፍላጎቱ እንዳላቸዉ ጠቅሰው በአጭር ጊዜ ውስጥ በጋራ መስራት የሚቻልባቸዉን ዝርዝር ጉዳዮች የያዘ ዕቅድ የሚያቀርቡ መሆኑን ተናግረዋል::
በመጨረሻም የፌዴሬሽኑ ሥራ አስኪያጅ አቶ ረመዳን አሸናፊ የኢትዮጵያ የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት ከስሩ ከ 600 በላይ ኤጀንሲዎች በአባልነት እንደመያዙ ፍላይ ናስ አየር መንገድ ተመጣጣኝ ክፍያና ጥራት ያለዉ አገልግሎት ካቀረበ አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን በመጥቀስ ፌዴሬሽኑና አባላት ኤጀንሲዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ጉዳዮች ወደፊት በፕሮፖዛሉ ላይ እንዲካተቱ አስገንዝበው ዕቅዱ ሲቀርብ ከፌዴሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ ጋር በመወያየት የሚፀድቅ መሆኑን ሀሳብ ሰጥተው ውይይቱ ተጠናቋል::

ፌዴሬሽን ጽ/ቤት

በብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ስር የሚገኘዉ ከከፍልሰት ተጎጂ ተመላሾች ድጋፍ እና ማቋቋም ጋር በተያያዘ የተቋቋመዉ የስራ ቡድን የአዋጅ 1178/2015 ማስፈጸሚያ መመሪያ እንዲሁም የስራ...
21/10/2023

በብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ስር የሚገኘዉ ከከፍልሰት ተጎጂ ተመላሾች ድጋፍ እና ማቋቋም ጋር በተያያዘ የተቋቋመዉ የስራ ቡድን የአዋጅ 1178/2015 ማስፈጸሚያ መመሪያ እንዲሁም የስራ ቡድኑን የ2016 የአንደኛ ሩብ አመት የስራ አፈፃፀምን የዉጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች ፌዴሬሽንን ጨምሮ የተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በተገኙበት ሪፖርት ቀርቧል::

ከሪፖርቱ በተጨማሪ ከፍልሰት ተጎጂ ተመላሾች ማቋቋምና ድጋፍ መስጠት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች ቀርቧል::

በፌዴሬሽኑ በኩል በስብሰባዉ ተሳታፊ የነበሩ የስራ አመራር ቦርድ የሆኑት አቶ ተፈራ ታደሰ እንዲሁም የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ ከፍልሰት ተጎጂ ተመላሾች ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ፌዴሬሽኑ ከሳዉዲ ተመላሽ የነበሩ ዜጎች ላይ የገንዘብ ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ሰልጥነዉ ህጋዊ በሆነ መልኩ መመለስ ለሚፈልጉ ዜጎች የስራ እድል ማመቻቸት የቻለ መሆኑን ጠቅሰው ፌዴሬሽኑ የበለጠ ተሳታፊ የሚሆንበት ሁኔታዎች እንዲመቻች ጠይቀዋል::

ከዚሁ ጋር ተያይዞ ክቡር አቶ ንጉሱ ጥላሁን አጋር አካላትን በማሳተፍ ቀጣይ ብዙ ስራዎችን እንደሚሰራ ገልፀዉ ፌዴሬሽኑ የተጋበዘበት አላማም የዚሁ አካል መሆኑን አንስተዋል::

ፌዴሬሽን ጽ/ቤት

https://youtu.be/-PvMF_5Ue2A?si=9hFZldiZO6ndPXGW
02/10/2023

https://youtu.be/-PvMF_5Ue2A?si=9hFZldiZO6ndPXGW

በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዘርፍ የተሰማራን ኤጀንሲዎች ልናውቃቸው የሚገቡ ፍቃዳችንን ሊያሰርዙ ወይም ሊያሳግዱን የሚችሉ ጥፋቶች ከ923/2008 አዋጅ አንፃር በግልፅ ተቀምጠዋል፡፡ ስለሆነም ....

Address

Gulf Aziz Building 4th Floor Room No. 404, Bole Medhanialem
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን:

Share