13/10/2021
Ethiopian Customs CommissionPublished - 2 days ago
አዲስ ዘመን እሁድ
መስከረም 30 ቀን 2014 ዓ.ም
በገቢዎች ሚኒስቴር ጉምሩክ ኮሚሽን
የሞጆ ጉምሩክ
ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
የተተው ዕቃዎች የዘራጅ ጨረታ ቁጥር
ሑ-03/2014 ጨረታ
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የሞጆ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስመጪዎችን በጉምሩክ አዋጅ 859/2006 አንቀፅ 51፤ ንዑስ አንቀፅ 1 እና በተሻሻለው የጉምሩክ አዋጅ 1160/2011 አንቀፅ 13 ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት ዕቃቸውን የጉምሩክ ሥነ-ተርዓትን ፈጸመው ባለመውሰዳቸው ዕቃዎቻቸውእንደተተዉ ተቆጥረዋል፡፡ ስለሆነምበገቢዎችሚኒስቴር ጉምሩክ ኮሚሽን የሞጆ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በጉምሩክ ቁጥጥር ሥር ያሉ ንብረቶች ሰለሚወገዱበት ሥርዓት ባወጣዉ መመሪያ ቁጥር 167/2012 አንቀጽ 9 መሠረት የተወረሱትን ንብረቶች ማለትም የተለያዩ የሆቴልና የቢሮ ዕቃዎች፣ ማሽኖች፣ ወረቀት፣ መኪናዎች፣ የፋብሪካ ጥሬ ዕቃዎች እና ሌሎች ዕቃዎችን በሀራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል :: በዚህም መሠረት ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለመጫረት የሚፈልጉና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን::
1. ተጫራቾች የዕቃዎቹን ዝርዝር፣ ዓይነት እና ብዛት በማስታወቂያ ሠሌዳ ላይ እና በአካል ለመመልከት ዘወትር ከሰኞ እስከ ሐሙስ ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 6፡00 ከሰዓት በኋላ ደግሞ ከቀኑ 7፡00 እስከ ቀኑ 10፡30 እና ዓርብ ከጠዋት 2፡00 እስከ ቀኑ 5፡00 ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 7፡30 እስከ ቀኑ 10፡30 እንዲሁም ቅዳሜ ከጠዋት 2፡00 እስከ ቀኑ 5:30 መመልከት ይቻላሉ፡፡
2.ተጫራቶች በጨረታ ከሚሸጠው ዕቃ ጋር የሚጣጣም በዘርፉ የፀና ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፤ 15% የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፡፡ ሆኖም ግምታዊ ዋጋው ከብር 500,000.00 በታች የሆነ ማንኛውንም ዕቃ ለመግዛት የ 15% የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ ሠርተፍኬት ማቅረብ ያስፈልጋቸው መወዳደር ይችላሉ፡፡
3 ማንኛውም ተጫራች ለጨረታው ማስከበሪያ የሚሆን ለሚጫረትበት ለያንዳንዱ ዕቃ ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺ) ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ CPO ጨረታው ከመከፈቱ በፊት በቅድሚያ ማስያዝ ይኖርበታል ፡፡ ተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙትን የጨረታ ማስከበሪያ አሸናፊው እንደታወቀ በ3 (ሶስት) የሥራ ቀናት ውስጥ የሚመለስላቸው ሲሆን አሸናፊ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያቸው ከአሸነፈበት ዋጋ ላይ የሚታሰብላቸው ይሆናል :: ተጫራቾች የሚያስይዙት CPO በቅርጫፍ ጽ/ቤቱ ስም ETHIOPIAN CUSTOMS COMMISSION MODJO BRANCH OFFICE በሚል ሲሆን የግል ባንክ ከሆነ ከአዲስ አበባ አስተዳደር ቅርጫፎች፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሆነ ደግሞ ከአዲስ አበባ አዳማና ሞጆ ቅርጫፎች መዘጋጀት አለበት::
4. የሀራጅ ጨረታው ተሳታፊ ተጫራቾች እያንዳንዳቸውን ዕቃዎች ለመግዛት የሚያቀርቡት በተራ ቁጥር 2 የተገለፁትን ማስረጃዎች ኮፒ እና ያቀረቡትን የመጫረቻ ዋጋ 300,000.00 (አንድ መቶ ሺ ብር) ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ CPO በማሰራት የጨረታው ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ8 ተከታታናይ ቀናት ጠዋት 4፡00 ድረስ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የውርስ መጋዘን አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ማስገባት ይቻላሉ፡፡