09/02/2026
በበጀት ዓመቱ ለ1 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር እየተሠራ መኾኑን ቢሮው አስታወቀ
የአማራ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ በበጀት ዓመቱ ለ1 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር እየተሠራ መኾኑን አስታውቋል፡፡
ቢሮው ይህን ያስታወቀው የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙን ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በገመገመበት ወቅት ነው።
የአማራ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኀላፊ ስቡህ ገበያው (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በክልሉ ያሉ የሥልጠና ኮሌጆች ብቁ እና በክህሎት የዳበረ ዜጎችን ከማፍራት አኳያ እየተወጡት ያለው ድርሻ ከፍ ያለ መኾኑን ገልፀዋል፡፡
በጀት ዓመት ለአንድ ሚሊዮን ዜጎች የሥራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ ርብርብ እተደረገ መሆኑን ገልጸው፤ ባለፉት ስድስት ወራት ለ6 መቶ 25 ሺህ ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉንም አመላክተዋል።
አጠቃላይ ከተፈጠረው የሥራ ዕድል ውስጥ ከ420 ሺህ በላይ የሚኾኑት በሲስተም በተዘረጋ አሠራር መኾኑን ም ነው ቢሮ ኀላፊ ስቡህ ገበያው (ዶ/ር) የገለፁት፡፡
ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር እና በቅንጅት በመሥራት ዜጎች ከራሳቸው አልፈው ለሌሎችም የሥራ እድል እንዲፈጥሩ በትኩረት ይሰራል ማለታቸውን ጠቅሶ የዘገበው አሚኮ ነው፡፡