10/02/2026
ተጨማሪ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን ለመቅጠር የወጣር ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን በመመልመል ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ከታች በተዘረዘሩት በአማራ ክልል በሚገኙ ምርጫ ክልሎች ላይ መሥፈርቱን የሚያሟሉ ተጨማሪ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን በመመልመል መቅጠር ስለሚፈልግ፤ የተያያዘውን ማስፈንጠሪያ https://nebe-election.org/recruitment በመጠቀም ከዛሬ ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ የካቲት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ እንድትመዘገቡ ቦርዱ ያሳውቃል። በምርጫ ክልል ጽ/ቤት ደረጃ ምዝገባ የሚካሄድበትን ቀን ቦርዱ ወደፊት ያሳውቃል።
የምልመላ መሥፈርት፡-
• ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣
• የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣
• የትምህርት ዝግጅት፦ 12ኛ እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣
• የሥራ ቦታ፦ ቦርዱ በሚያቋቁማቸው የምርጫ ጣቢያዎች፣
• የክልሉን የስራ ቋንቋ መናገር እና መጻፍ የሚችሉ
• የሥራ ቆይታ ፦ ለሁለት ወር፣
• ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም.