ትኩስ የስራ እና ጨረታ ማስታወቂያዎች

ትኩስ የስራ እና ጨረታ ማስታወቂያዎች በዚህ ገጽ በየቀኑ የሚወጡ የስራ ማስታወቂያዎች፣ ጨረታዎች እና ሌሎች ልዩ ልዩ ትኩስ ማስታወቂያዎች ይቀርቡበታል።
(8)

💻 በቴክኖሎጂ ወገኖቻችንን እንፈልግ!ትናንት በምሥራቅ አርሲ በአሰኮ ወረዳ የተከሰተውን አሳዛኝ ሁኔታ ተከትሎ፣ የጠፉ ወገኖቻችንን ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚያገናኝ ቀላል የቴሌግራም ቦት (Bot)...
03/06/2026

💻 በቴክኖሎጂ ወገኖቻችንን እንፈልግ!

ትናንት በምሥራቅ አርሲ በአሰኮ ወረዳ የተከሰተውን አሳዛኝ ሁኔታ ተከትሎ፣ የጠፉ ወገኖቻችንን ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚያገናኝ ቀላል የቴሌግራም ቦት (Bot) በዲጂታል ባለሙያዎቻችን አዘጋጅተናል።
በአሁኑ ሰዓት በርካታ የደረሱበት ያልታወቁ ሰዎች በመኖራቸው፣ ይህ መድረክ መረጃዎችን በአንድ ቦታ ሰብስቦ በፍጥነት ለማገናኘት ይጠቅማል።

የቦቱ ሊንክ፦

እንዴት መጠቀም ይቻላል?
ሊንኩን ተጭነው በመግባት Start የሚለውን ይጫኑ።

ቤተሰብ የሚፈልጉ ከሆነ "ቤተሰብ ፈላጊ ነኝ" የሚለውን ቁልፍ ተጭነው ፎርሙን ይሙሉ Telegram በራስ-ሰር ይመራዎታል።

ስለ ጠፉ ወይም ስላሉ ወገኖች ማንኛውም መረጃ ካለዎት "መረጃ አለኝ" የሚለውን ተጭነው ያጋሩን።

ለስራ ፈላጊ ወጣቶች ጥሪ፦ በቦቱ የሚመጡ መረጃዎችን በፈቃደኝነት ለመለየት፣ ለማጣራት (Data Verification) እና ለተጨነቁ ቤተሰቦች በስልክ ደውሎ መረጃውን ለማድረስ የምትፈልጉ ተመራቂዎች በውስጥ መስመር አግኙን።

እባክዎ ይህ መልዕክት ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ የዜግነት ድርሻዎን ይወጡ። እውቀታችን ለወገናችን ድምፅ ይሁን!

ክቡራን ተከታተዮቻችን፤ ገጻችን የስራ ማስታወቂያዎችን እና የቴክኖሎጂ መረጃዎችን የሚያጋራ ቢሆንም፣ በምሥራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንፁሃን ወገኖቻችን ላይ የደረሰው አሰቃቂ ጭፍጨፋ እና መፈናቀ...
02/06/2026

ክቡራን ተከታተዮቻችን፤ ገጻችን የስራ ማስታወቂያዎችን እና የቴክኖሎጂ መረጃዎችን የሚያጋራ ቢሆንም፣ በምሥራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንፁሃን ወገኖቻችን ላይ የደረሰው አሰቃቂ ጭፍጨፋ እና መፈናቀል እጅግ አሳዝኖናል።

እንደ አንድ የቴክኖሎጂ ባለሙያ/ማህበረሰብ፣ ከተጎዱት መካከል ከ280 በላይ የጠፉ ሰዎችን ለመፈለግ እና ለመርዳት የሚያግዝ የዲጂታል መድረክ (የፍለጋ ቦት/ድረ-ገጽ) በነፃ ለማልማት እያሰብን ነው። በዚህ አካባቢ ያላችሁ ወይም ታማኝ መረጃ ማድረስ የምትችሉ ወገኖች በውስጥ መስመር (Inbox) እንድታግዙን በትህትና እንጠይቃለን።
ለሟቾች ፈጣሪ ገነትን እንድያወርሳቸው ለዘመድ አዝማድ መጽናናትን እንመኛለን።

"እኔ እኮ ተምሬያለሁ፣ ታዲያ ስራ ለምን አላገኘሁም?!"ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀው ስራ አጥተው ቤት መቀመጥ የብዙዎቻችን መራራ ህመም ሆኗል። ነገር ግን ማንም የማይነግረን እውነተኛው ምክንያት ምን...
01/06/2026

"እኔ እኮ ተምሬያለሁ፣ ታዲያ ስራ ለምን አላገኘሁም?!"

ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀው ስራ አጥተው ቤት መቀመጥ የብዙዎቻችን መራራ ህመም ሆኗል። ነገር ግን ማንም የማይነግረን እውነተኛው ምክንያት ምንድን ነው?
ችግሩ የስራ መታጣቱ ነው ወይስ የእኛ አደገኛ አስተሳሰብ?
ለአናጺው አንቶኒዮ የተነገረው ምስጢርስ ምን ነበር?

📌 በድረ-ገጻችን ላይ ብዙዎችን ያስቆጣውን፣ ያከራከረውን እና እውነተኛውን መፍትሄ ያመላከተውን አዲስ ጽሑፍ አሁኑኑ ያንብቡ። የእርስዎንም አስተያየት በኮሜንት ያጋሩን!

👇 ሊንኩን ተጭነው ሙሉውን ያንብቡ፡ 🌐 https://l1nq.com/k4al9u3

30/05/2026

‼️ የስራ ማስታወቂያ ‼️
🏢 የድርጅቱ ስም = ትዊንክል የልጆች መጫወቻ
📌 አድራሻ = መገናኛ፣ ከደራርቱ ታወር ጀርባ፣ ቱሪስት ሳይት 40/60 ኮንዶሚኒየም
💼 የስራ መደብ = የመጫወቻ ስፍራ ሁለገብ ሰራተኛ (ደንበኞችን መቀበልና ልጆችን እንዴት እንደሚጫዎቱ መርዳት)
🎓 ትምህርት = አያስፈልግም
🗓 የስራ ልምድ = በአገልግሎት ሰጪ ድርጅት 1 ዓመት የስራ ልምድ
ከልጆችን ጋር መጫወትነ‍ኣ መንከባከብ የምትወድ
የስራ ሰዓት ጠዋት 3:00 - ማታ2:00
🚻 ፆታ = ሴት
🚻 እድሜ 18 እስከ 25 አመት
🕒 የስራ አይነት = ሙሉ ቀን
👥 የሚፈለጉ ሰራተኞች ብዛት = 1
💰 ደመወዝ = በስምምነት
📩 ለማመልከት = በስልክ 0923563371 ወይም 0944121769 ይደውሉ
📞 የመገናኛ መረጃ = 0923563371 ወይም 0944121769 / [email protected]
የንግድ ፈቃድ ያልው ነጋዴ ውይም የግል ወይም የመንግስት ሰራትኛ ተያዥ ያላት

ሰፈሯ መገናኛ፡ ጉርድ ሾላ፡ ሾላ፡ ሀያ አራት፡ ሀያ አራት ወይም ለስራ ቦታው ቅርብ ለሆነች ብቻ

የስራ ማስታወቂያ
19/05/2026

የስራ ማስታወቂያ

19/05/2026

ኤስ ኤም ኃ/የተ/የግ/ማህበር ቀጥሎ የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟላ ሠራተኛን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
የስራ መደብ: ጁንየር የቢሮ ረዳት እና አስተባባሪ (Junior Office Assistant & Coordinator)
የቅጥር ሁኔታ፡ ኮንትራት ሆኖ እንደሁኔታው የሚራዘም
የት/ት ደረጃ፡ በማርኬቲንግ፣ በሴክሬተሪያል ሳይንስ ወይም በተዛማጅ መስኮች ዲፕሎማ ወይም ዲግሪ ያላት
የሥራ ልምድ፡ 0 ዓመትና ከዚያ በላይ
ጾታ፡ ሴት
ዋና ዋና የስራ ኃላፊነቶች
የቢሮ ስራዎች፡ ከባለሙያዎች የሚላኩ ፋይሎችን እና የንድፍ ስራዎችን ፕሪንት ማድረግ፣ ሰነዶችን በስርዓት መያዝ እና ደንበኞችን ማስተናገድ።
የውጭ ስራዎች፡ ቢሮውን ወክሎ ወደ ተለያዩ ተቋማት በመሄድ የቢሮ ጉዳዮችን በቅልጥፍና ማስፈጸም እና መከታተል።
ማስተዋወቅ እና ውል፦ የቢሮውን አገልግሎቶች ለደንበኞች ማስተዋወቅ እና የውል ስምምነቶችን ማመቻቸት።
ችሎታ፡ መሰረታዊ የኮምፒውተር (Word, Excel) እውቀት ያላት፣ ቀልጣፋ፣ የንግግር እና የተለያዩ ተቋማት ጋር ሄዶ ጉዳይ የማስፈጸም ብቃት ያላት።
ደሞዝ፡ በስምምነት
የስራ ቦታ: አዲስ አበባ, ሀያት አደባባይ
ከስራው ሁኔታ አንፃር የመኖሪያ አድራሻዋ ለስራ ቅርብ ቢሆን ይመረጣል!
ለማመልከት
በቴሌግራም ሊንክ ማመልከት ወይም
በአካል በመቅረብ የትምህርትና ተያያዥ ማስረጃ ኮፒ በማቅረብ መመዝገብ ይችላሉ፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ ይደውሉ!
☎️ 0991473978

For Electrical Engineers omly!
26/03/2026

For Electrical Engineers omly!

ተጨማሪ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን ለመቅጠር የወጣር ማስታወቂያየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን በመመልመል ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ...
10/02/2026

ተጨማሪ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን ለመቅጠር የወጣር ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን በመመልመል ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ከታች በተዘረዘሩት በአማራ ክልል በሚገኙ ምርጫ ክልሎች ላይ መሥፈርቱን የሚያሟሉ ተጨማሪ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን በመመልመል መቅጠር ስለሚፈልግ፤ የተያያዘውን ማስፈንጠሪያ https://nebe-election.org/recruitment በመጠቀም ከዛሬ ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ የካቲት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ እንድትመዘገቡ ቦርዱ ያሳውቃል። በምርጫ ክልል ጽ/ቤት ደረጃ ምዝገባ የሚካሄድበትን ቀን ቦርዱ ወደፊት ያሳውቃል።

የምልመላ መሥፈርት፡-

• ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣

• የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣

• የትምህርት ዝግጅት፦ 12ኛ እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣

• የሥራ ቦታ፦ ቦርዱ በሚያቋቁማቸው የምርጫ ጣቢያዎች፣

• የክልሉን የስራ ቋንቋ መናገር እና መጻፍ የሚችሉ

• የሥራ ቆይታ ፦ ለሁለት ወር፣

• ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም.

የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የመምህራን እና ቴክኒካል አሲስታንስ የስራ ማስታወቂያ
26/01/2026

የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የመምህራን እና ቴክኒካል አሲስታንስ የስራ ማስታወቂያ

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የስራ ማስታወቂያ
24/01/2026

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የስራ ማስታወቂያ

Address

Amhara
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ትኩስ የስራ እና ጨረታ ማስታወቂያዎች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share